Sunday 18 May 2014

ዜና ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ: መዝሙር አለቀሰ

ዜና ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ: መዝሙር አለቀሰ

መዝሙር አለቀሰ

መዝሙር አለቀሰ
የያሬድ ዝማሬ፣ የአዘማመር ስልቱ
የበገናው ቃና፣ማሲንቆ ቅኝቱ
የከበሮው ውበት የዋሽንት ፍሰቱ፡


ነበር ተፈጥሯቸው ስብሐት ሊዘሩ
ሥርዓት ሊያከብሩ
መንፈስን አድሰው ውበት ሊደምሩ
ምህላ ሊያደርሱ ኑዛዜ ሊያወሩ
ስንዱዋ እመቤት ቤተ ክርስቲያን ቅድስት
እንዳላስተማረች ሁሉን በሥርዓት


ዛሬማ አፍ የፈታ ሁሉ እያንጎራጎረ፣
ቀኖና ትውፊቱን እየሸረሸረ
የመዝሙር ሥርዓቱ ስልቱ ተቀየረ
መዝሙር ዜማ ሳይሆን ጩኸት ሆኖ ቀረ
ለነፍስ ሐሴት ትቶ ለሥጋ አደረ


ሳኦልም ከደዌው እንዳልተፈወሰ
ወኅኒውም በመዝሙር እንዳልፈራረሰ
መዝሙር ቅዱሳንን እንዳላወደሰ
ዜማን ሐዘን ገባው መዝሙር አለቀሰ


ንጉሥ ገብረ መስቀል ጦር ከእግር ሰክቶ
በፍጹም ተመስጦ አለምን ረስቶ
እንዳልነበር ሁሉ ጸጋችን ምግባችን
መዝሙር አንገት ደፋ ከመላእክት በላይ አዋቂዎች ሆነን


ሳይጠፋ መዝሙሩ እስከ ሥርዓቱ
ፈር እየለቀቀ ዘማሪ ነኝ አለ ሁሉም በየቤቱ
በጠፋበት ሁሉ ተሰጥኦው መክሊቱ
መዝሙር አለቀሰ ተገፍቶ መብቱ
ተጥሶ ሥርዓቱ።
ምንጭ
ገድለ ቅዱሳን Gedle Kidusan Acts of Kidusan

Friday 16 May 2014

ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተ ክርስቲያን

መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ

ብዙዎች ኢየሱስ ክርስቶስን ቤተ ክርስቲያን እንደማትሰብክ አድርገው ለማቅረብ ይሞክራሉ፤ ነገር ግን ሐዋርያዊት የኾነችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ስለክርስቶስ ያላስተማረችበት ጊዜ የለምም አይኖርም፤ ደግሞም እናት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በጊዜያችን አንዳንዶች መናፍቃን የኢየሱስን ክብር አሳንሰው ከአብ በታች አድርገው እንደሚያስተምሩት ሳይኾን በእውነት ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክብሩ የተካከለ፣ ቅድመ ዓለም የነበረ አኹንም ያለና ዓለምን አሳልፎ የሚኖር፤ ለፍርድ ዳግመኛ የሚመጣ፤ እውነተኛ ፈራጅ የአማልክት አምላክ የነገሥታት ንጉሥ ነው ብላ የምታስተምረው፡፡ ይኽ ብቻ ሳይኾን ሥጋውን ደሙን በምትሠዋበት በቃል ኪዳን ታቦቱም ላይ “ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው” (የሕያው የአብ የባሕርይ ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ) ብላ አክብራ ስሙን ትጽፋለች እንጂ በድፍረት ሆና ስሙን መቀለጃ አታደርግም፡፡

Monday 21 April 2014

ከትንሣኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ

በመቅደስ ተስፋዬ

ሰኞ- ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡

ማግሰኞ- ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29

ረቡዕ- አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡ 

ሐሙስ- አዳም ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡

አርብ- ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡

ቅዳሜ- ቅዱሳት አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡

እሁድ- ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡ -

መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንላችሁ -

Saturday 19 April 2014

ትንሣኤ ዘክርስቶስ - የክርስቶስ ትንሳኤ

ሦስት መዓልት እና ሦስት ሌሊት በመቃብር፤
ሦስት መዓልት እና ሦስት ሌሊት የሞላው እንዴት ነው?፤
እንዴት ተነሣ?
ለምን በአዲስ መቃብር ተቀበረ?
እንዴት በዝግ መቃብር ተነሣ?
መቃብሩን ማን ከፈተው?

(መልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው/ PDF):- ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስክርስቶስ ድኅነተ ዓለምን በመስቀል ላይ ከፈጸመ በኋላ በአካለ ሥጋ ወደ መቃብር ወረደ÷ ይኸውምበመቃብር ፈርሶ በስብሶ መቅረትን ሊያስቀርልን ነው፡፡ በአካለ ነፍስ ደግሞ ወደ ሲኦል ወረደ÷ይኸውም በሲኦል ለነበሩ ነፍሳት ነፃነትን ይሰብክላቸው ዘንድ ነው፡፡ መለኮት፥ በተዋሕዶ፥ ከሥጋምከነፍስም ጋር ነበረ፡፡ ለዚህ ነው፥ መቃብር ሥጋን ሊያስቀረው ያልቻለው፤ ሲኦልም ነፍስን ማስቀረትአልተቻለውም፡፡

Tuesday 15 April 2014

ከአንድ ፕሮቴስታንት እህታችን የደረሰን ጥያቄ

በአሸናፊ መንግስቱ

ኦርቶዶክሶች የዳናችሁት በክርስቶስ ሞት ሆኖ ሳለ በሞቱ ታዝናላቹ፤ ክርስቶስ ባይሰቃይ አትድኑም ነበር ስለዚህ በስቃዩ መደሰት ሲገባቸሁ ለምን ታዝናላቹ?

መልሱን በአጭሩ ለመመለስ ያህል :-በመዳናችን እንዲሁም በትንሣኤው እንጂ በሞቱ አንደሰትም! ለምን የሚለውን ለማወቅ ህሊና ብቻ ይበቃልና አንድ ቀለል ያለ ምሳሌ ሰጥተን እንመልከተው፡-


እጅግ በጣም ከሚወድህ ወዳጅህ ጋር አብረህ በመንገድ ላይ እየተጓዝህ ሳለ አድብቶ ይጠብቅህ የነበረ ጠላት መሳሪያ አውጥቶ ወዳንተ ይተኩሳል ልብ በል መሳሪያው የተተኮሰው ላንተ እንጂ ለወዳጅህ አይደለም መሳሪያው ካገኘህም ያለጥርጥር ትሞታለህ ነገርግን ወዳጅህ ካንተ ቀድሞ የመሳሪያውን መተኮስ አይቶ ነበርና ደረቱን ሰጥቶ ከፊትህ ቆመ መሳሪያውም ደረቱ ላይ አረፈችና ወዳጅህ ስላንተ ሞተ፤ አንተን አድኖ ሞተ፤ አሁን አንተ በህይወት ያለኸው ወዳጅህ ስለሞተልህ ነው፡፡

እናማ አሁን አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ አንተ የምትደሰተው በወዳጅህ መሞት ነው ወይስ በመዳንህ? መቼም ወዳጄ ለኔ ሲል ሞቷልና ሞቱ ያስደስተኛል ካልክ አንተ ጠላቱ እንጂ ወዳጁ አይደለህም ከምንም በላይ ደግሞ ራስ ወዳድ መሆንህን ያሳያል፡፡ እኛ ግን በወዳጃችን ሞት እናዝናለን፤ በህይወት ስለመኖራችን ደግሞ እንደሰታለን፤ ወዳጃችን ስለኛ ስለተቀበለው ህመም፤ ስላቃሰተው ማቃሰትም በዘመናችን ሁሉ እያሰብነው እናዝናለን፤ በዚህም ወዳጃችን ለእኛ የከፈለውን ዋጋ ማወቃችን ይገለጻል::

አባቶቻችን እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ጥበብ ይልቅ ዓለምን ያዳነበት ይበልጣል እንዲሉ ነገሩን ቀለል አድርጎ ለማሳየት እንጂ ይህ ምሣሌ በምንም አይነት የክርስቶስን የማዳን ጥበብ አይገልፅም፡፡

እንግዲህ ለሥጋዊ ወዳጃችን እንዲህ ካዘንን አንዳች ኃጢያት ሳይኖርበት ስለተንገላታው ስለክርስቶስ ስቃይ እንዴት አናዝን? የእርሱን ግርፋትና መንገላታት እያሰበ ስለማልቀስ ፋንታ የሚስቅስ እንዴት ያለ ኃጢያተኛ ነው? የእርሱን መቸንከር እያየ ያለኃጢያቱ የማይሞተው ሲሞት እየተመለከተ ስለማዘን ፈንታ የሚደሰትስ እንዴት ያለ ክርስቲያን ነው? በስቃይ የሚደሰትስ እንዴት ያለ ሰው ነው?

የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት መዳኛችን እንደሆነ እናምናለን ነገር ግን ስለመዳናችን እንደሰታለን እንጂ ስለስቃዩና ስለሞቱ ግን አብዝተን እናዝናለን ዳግም ደግሞ በትንሣኤው ታላቅ ሀሴትን እናደርጋለን፡፡

እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የቀደመችው እውነተኛይቱ መንገድ!!!!

‹‹ሰሙነ ሕማማት››


በዲ/ን ህብረት የሺጥላ
‹‹ሰሙነ ሕማማት›› መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓት ነው፡፡ በርካታ ሰዎች ቤተ ክርስቲያንን ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ የምትጓዝ አካል አድርገው ሊገልጧት ይሞክራሉ፡፡ ይህ እጅግ አላዋቂ መሆናቸውን ይመሰክራል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከመጽሐፍ ቅዱስ ያልተገኘና በሥጋዊና በደማዊ ዕውቀት ላይ የተመሠረተ ሥርዓት የላትም፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ‹‹ከሕማማቱ በኋላ›› በማለት ስለ ሰሙነ ሕማማት የሚያወሳ ቃል ተጠቅሟል፡፡ (የሐዋ1.3) ሰሙነ ሕማማት የሁለት ቃላት ጥምር ውጤት ነው፡፡ ‹‹ሰሙን›› የሚለው ቃል ‹‹ሰመነ›› ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ስምንት ቀኖች ወይም ሳምንት ማለት ነው፡፡ ‹‹ሕማማት›› የሚለው ቃልም እንደዚሁ ‹‹ሐመመ›› ወይም ‹‹ሐመ›› ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን መከራዎች ማለት ነው፡፡ ‹‹ሕማማት›› የምንለው ለብዙ ሲሆን ነው፡፡ ለአንድ ወይም ለነጠላ ሲሆን ደግሞ ‹‹ሕማም›› እንላለን፡፡ እንግዲህ ሁለቱን ቃላት በማናበብ ‹‹ሰሙነ ሕማማት›› ስንል ‹‹የመከራዎች ሳምንት›› ማለታችን ነው፡፡

በግብረ ሕማማት ውስጥ የሚነገሩ ባዕድ ቃላት


Saturday 12 April 2014

አዎ ማኅበረ ቅዱሳንን ተጠንቀቁ! ትልቁ ስጋት እሱ ነውና


በአዲሱ ተስፋዬ

መነሻ

ይህንን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ሰንደቅ ጋዜጣ በሚያዝያ 1/2006 ዓ.ም እትሙ ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ያወጣው ቃለ መጠይቅና ሀተታ ነው [i] :: ሶስቱም አስተያየት ሰጭዎች “ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ነው:: ስለዚህም መንግስት ሊያፈርሰው ነው ” የሚለው ወቅታዊ ዜና ምንጩ ከየት እንደሆነ ግልጽ እንዳልሆነ ጠቅሰዋል :: በፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አበበ ወርቁ ጉዳዩን “በሬ ወለደ ነው” ብለው ሲያጣጥሉት ፣ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ደግሞ ” የዚህ ወሬ ምንጩ ከየት እንደሆነ አናውቅም” ሲሉ ተመሳሳይ ነገር ተናግረዋል።

Wednesday 2 April 2014

የጎልማሶችና ወጣቶች ማኅበራት ኅብረቱ በቤተ ክርስቲያን ስም የሚፈጸሙ ሕገ ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር መዘጋጀቱን አስታወቀ፤ በወጣቶቹ ዝግጅት የተደናገጡ የለውጥ ተቃዋሚ አማሳኞች የኅብረቱን እንቅስቃሴና አመራሮቻቸውን በሽብር ለመወንጀል እያሤሩ ነው

ቁጥጥር ከሚደረግባቸው ሕገ ወጥ ተግባራት መካከል÷ ያልተፈቀደላቸው ሰባክያን ስምሪትና የኅትመት ውጤቶቻቸው ሽያጭና ስርጭት፣ የአስመሳይ ባሕታውያንና መነኰሳት ነውረኛ ድርጊቶች፣ ሕገ ወጥ ልመና፣ የአጥቢያ አስተዳደር ሙስናና የወጣት ሱሰኝነት ይገኙበታል፡፡
ማዕተብ ያለው ኦርቶዶክሳዊ ምእመን በተለይም ወጣቱ ከሱስ ነጻ መኾን አለበት፤ መስቀሉን አንጠልጥሎ በየባንኮኒውና በየዳንኪራው ከመታየት መጠበቅ አለበት፤ ዶግማውን፣ ቀኖናውንና ትውፊቱን ያወቀና የጠነቀቀ፣ በኢኮኖሚያዊና ፋይናንሳዊ አቅሙም ጠንካራና እርስ በርሱ መደጋገፍ ይገባዋል፡፡
102 ያኽል ማኅበራት አንድነት የፈጠሩበትና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አቅራቢነት የቅ/ሲኖዶሱን ዕውቅና ያገኘው ኅብረቱ ከ150,000 በላይ አባላት አሉት፡፡ የኅብረቱ አመራሮችና አባላት፣ ወቅቱ ከሰንበት ት/ቤቶች አንድነትና ከማኅበረ ቅዱሳን ጋራ በፍቅር እስከ መጨረሻው የምንቆምበት ነው ብለዋል፡፡
‹‹ቤተ ክርስቲያን ተጨንቃ ትጣራለች፤ የምትጣራው ወጣቱን ነው፤ ወጣት ዕውቀትና ጉልበት አለው፤ እኔ ሴቷን ጨምሮ ኹላችን እያንዳንዳችን ሓላፊነት አለብን፤ ወይ ግዴታችሁን ተወጡ ወይ ውረዱ የምንልበት ወቅት ነው!!›› /የማኅበራት ኅብረቱ ሰብሳቢ ወ/ሪት ፌቨን ዘሪሁን/

(ኢትዮ – ምኅዳር፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፷፪፤ መጋቢት ፳፬ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.)

የይሁዳ ክህደት ለ30 ዲናር፣ የእነዚህ ደግሞ የማኅበረ ቅዱሳንን ሀብት ለመዝረፍ

(ደጀ ሰላም፣ መጋቢት 22/2006 ዓ.ም፤ ማርች 31/2014. PDF)፦ የአስቆሮቱ ይሁዳ ጌታችንን አሳልፎ ሰጠው። ምህሩንና ጌታውን ክዶ፣ ስሞ ለግርፋት እና ለመስቀል ሞት ተስማማ። ይህንን የጌታን ሕማማት፣ ስቅላት፣ ሞትና ትንሣኤ በምናስብበት በአሁኑ ወቅት ማኅበረ ቅዱሳንን ለሕማም፣ ለስቅላት እና ለሞት አሳልፎ ለመስጠት የሚደረገው ትርምስ ተጀምሯል። ይሁዳ ለ30 ዶላር እነዚህ የዘመናችን ሰቃልያን ደግሞ “ማኅበሩ ያፈራውን ሀብት በሙሉ ለመዝረፍ ጊዜው አሁን ነው” ብለዋል። በዚህም በዚያም ክህደት እና ስቅለት።

Monday 31 March 2014

ማኅበረ ቅዱሳንን ለምን ጠሉት??


READ IN PDF
አባ ሰላማ በማለት በቅዱሳን ስም እየተጠራ ቅዱሳን መላእክትን፣ እመቤታችንን እና ጻድቃንን የሚዘልፈው “አባ ሰላማ” የተሰኘው የተሐድሶ መናፍቃን ብሎግ፤ በማያፍር አንደበቱ ማኅበረ ቅዱሳንን በመሳደብ ላይ ይገኛል:: ማኅበረ ቅዱስንም “የቅዱሳኑ የስድብ በረከት ለእኔም ይድረሰኝ” በማለት ይመስለናል ለብሎጉ ምን ዓይነት መልስ ሰጥቶ አያውቅም::

“አባ ሰላማ” ብሎግ በ1992 ዓ/ም ከቤተ ክርስቲያ ተወግዘው የተለዩት የተሐድሶ መናፍቃን በድሬዳዋዎቹ ቡድን እንደሚመራ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ::

ማህበረ ቅዱሳን


ከታምራት ፍሰሃ
በአገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ት/ት ተቋም ተማሪወችን አሰባስቦ ስላስተማረ ፡ ብዛት ያላቸውን በግእዝ የተፃፉ መፃህፍትን ተርጉሞ ፡ ለወጣቱ የሚጠቅሙና የሚያንፁ መፃህፍትን አሳትሞ ስላቀረበ ፡ እጅግ የበዙ ገዳማትን አድባራትን ስለረዳ ፡ የአብነት ተማሪወችና አስተማሪወች ራሳቸውን እንዲችሉ እጅግ ብዙ ፕሮጄክቶችን ቀርፆ በተግባር ስላዋለ ፡ የፈረሱ አብያተ ክርስቲያናትን ስላሳነፀ ፡ ብዙ ሺህ ኢአማንያንን በፈቃዳቸው አስተምሮ እንዲጠመቁ ስላስተባበረ ፡ የካህናት ማሰልጠኛወች በየቦታው እንዲቋቋሙ ስላስተባበረ ፡ አፅራረ ቤተክርስቲያንን ነቅቶ ስለጠበቀ ፡ የመናፍቃንን ክፉ አላማ ለሁሉ ዘወትር ግልፅ ስላደረገ ፡ ቤተክርስቲያንን ከተሃድሶወች ስለተከላከለ ፡ የክርስቶስን ወንጌል በየገጠሪቷ ክፍል እየዞረ ስላስተላለፈ ፡ ወጣቶች በነፃ ያለምንም ክፍያ ቤተክርስቲያንን እንዲያገለግሉ አርአያ ስለሆነና ስላስቻለ ፡ በጣም ርቀው የነበሩ ክርስቲያኖችን አቅርቦ ለቤተክርስቲያን በሙያቸው እንዲያገለግሉ ስላስተባበረ ፦አክራሪ ከተባለ እንግዲህ እኔም አክራሪ ልባል እወዳለሁ!!!

ከሙስና መራቅ ፡ ሃገርን መውደድ ፡ ቤተክርስቲያንን ማወቅ ፡ ክርስቶስን ማምለክ አክራሪ ካስባለ እኔም አክራሪ ተብየ እንድከሰስ እወዳለሁ!!!

ቦንብ ሳልወረውር ቦንብ የሚወረዉሩትን አስቀድሜ አይቼ ወገኖቼን እንዳያጠፉ ማሳሰቢያ መስጠቴ አክራሪ ካስባለኝ ፡ እንዲህ ያለ አክራሪነቴን እወደዋለሁ!!!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ትክክል ናት ፡ ክርስቶስም መሰረቷ ነው ፡ ድንግል ማርያምም ክብሯ ናት ማለት አክራሪ ካስባለ ፡ አክራሪ ተብሎ መሞት ክብር ነው!!!

ክርስቶስን በካደ ትውልድ መካከል ፡ በዲያቢሎስ በምትደምቅ አለም ለመዋብ በሚቋምጥ ሰው መካከል እውነት እውሽት መስላ መወቀሷ ፡ ውሽትና ክፋትም ከሚሰሯት ጋር መከበሯ የሚጠበቅ ነው፡፡

ዲያቢሎስ የተጣባት ክርስቶስ የራቃት ህሊና ፦ የገደላትን እየሾመች የሞተላትን መጥላቷ የሚጠበቅ ነው፡፡

ነገር ግን ፦ እኛ ከዚህ ህብረት አለመሆናችን ይታወቅ ዘንድ : አንድም እውነት ስለሆነው ስለጌታችን ስለክርስቶስ ምስክርነት ከእውነት ጎን እንቆማለን፡፡

ማቴ 5፡11 “ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ።”

የማን መጨረሻ? የማኅበረ ቅዱሳን? ወይስ… የኢህአዴግ የመጨረሻ መጀመሪያ?

  • አቶ መለስ ዜናዊና አቦይ ጸሀዬ ከደርግ በተሰነዘረባቸው ጥቃት ገዳማውያን አባቶች የመነኮሳትን ልብስ በማልበስ ከሞት አድነዋቸዋል፡፡(ደርሶ ጡት ነካሽ ቢሆኑም)
  • ‹‹ቤተ ክርስቲያኗ ተከታዮቿን፣ ለነበረው የኢትዮጵያ መንግሥት እንዲገዙ ከማስተማር በዘለለ የብሔራዊንቃት(ማንነት) ማስተማርያም ነበረች፡፡ ዶ/ር አረጋዊ
  • ‹‹መንግሥት ያግዘኛል ብዬ ነው እዚህ መንበር ላይ የተቀመጥኩት፤ ባያግዘኝ ሥልጣኑን አልቀበልም ነበር››አቡነ ማትያስ
  • ፓትርያርኩ የመዘንጋት፣ ለውሳኔ የመቸገር፣ ዕንቅልፍ የማብዛትና መሰል ችግሮች ሥራቸውንእያስተጓጎሉባቸው እንደኾነ ይነገራል፤ ራሳቸውም ‹‹ሲጨንቀኝ እተኛለኹ፤ ስተኛ ደግሞ እረሳዋለሁ››በማለት ችግሩን አምነው ተቀብለዋል፡፡
  • ‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስን ይመለከታል›› በሚል ርእስ ለደኅንነቱ ዋና መሥ/ቤት የተላከ ደብዳቤ…(ያንቡት)
  • ‹‹እናቋርጣለን፤ ነገር ግን ‹እናንተ የጸጥታ ስጋት አለ› ብላችሁ በደብዳቤ ሓላፊነቱን ውሰዱ፡፡ እኛምለካህናቱ ለምእመናኑ ሁኔታውን ዘርዝረን እንገልጻለን›› አቡነ እስጢፋኖስ መዋቅራዊ ጥናቱ ይቁም በማለት ለመጣ የመንግሥት ካድሬ ሰጡት መልስ…

Wednesday 26 March 2014

የ‹‹አክራሪነትና የጽንፈኝነት›› ታፔላ ለጠፋ ከምን ተነሳ ? አሁን ምን ደረጃ ላይ ይገኛል ?

(አንድ አድርገን መጋቢት 17 2006 ዓ.ም)፡- የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በህይወት ከማለፋቸው በፊት በመጨረሻ የፓርላማ ቆይታቸው ላይ ስለ ሀገሪቱ ወቅታዊ ጉዳይ የተናገሩት ነገር ነበር ፤ ነበሩ ሳይባሉ በፊት የመንግሥታቸውን አቋም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለህዝቡ አስተላልፈዋል ፤ ይህን ንግግር ከተናገሩ በኋላ ግን ዳግም ለ20 ዓመት በተቀመጡበት የፓርላማ ወንበራቸው ላይ ተቀምጠው ሳናያቸው ወደ ማይቀረው መንገድ ተጉዘዋል ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እሳቸው ከመናገራቸውም በፊትም ሆነ በኋላ መንግሥት ስለ አክራሪነትና ጽንፈኝነት ጉዳይ በ”አዲስ ራዕይ” መጽሔት ፤ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ፤ በኢትዮጵያ ሬዲዮ እና በብቸኛው የመንግሥት እስትንፋስ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ብዙ ነገሮችን ብሏል ፤ ዘጋቢ ፊልምም እስከ መሥራት ደርሷል፡፡ ያለፈውን አንድ ዓመት የመንግሥትን ዝምታ መሰረት አድርገው መንግሥት ይህን አቋም የቀየረ የሚመስላቸው ሰዎች አሉ፡፡ ሳይታሰብ የተከሰተው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት በኋላ የሀዘን ጊዜው በመርዘሙ የተነሳ ቀድሞ አቋም የተያዘባቸው አጀንዳዎች ሳይራገቡ ተከድነው መቆየታቸው እንጂ በመንግሥት በኩል አቋሙን የለወጠበት ነገር አልተመለከትንም፡፡ ገዥው ፓርቲ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ያንጸባርቁትን አቋም ሳይቀንስ ሳይጨምር ለማስቀጠል እየሰራ ይገኛል ፤ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትርም በተሰየሙበት እለት “እናስቀጥላለን” ብለው ነበር የተናገሩት፡፡ እስኪ ይህ የአክራሪነትና የጽንፈኝነት ታፔላ ለጠፋ ጉዳይ የመንግሥት አቋም ከምን ነጥብ እንደተነሳ ፤ አሁን ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ እንቃኝ…

Saturday 22 March 2014

ሰበር ዜና – የማኅበረ ቅዱሳንን አመራርና አባላት በአክራሪነት የሚከስ ዶክመንተሪ ሊዘጋጅ ነው ተባለ

  • ዶክመንተሪው የ2007 ሀገራዊ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት አካል እንደኾነ ተጠቁሟል
  • ‹‹ማስረጃ አቅርቡና እንነጋገርበት›› ለሚለው የማኅበሩ ጥያቄ ምላሽ አልተሰጠም

(ፋክት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፴፰፤ መጋቢት ፳፻፮ ዓ.ም.)



በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሲኖዶሱን ይኹንታ አግኝቶ በመላው አገሪቱ የሚንቀሳቀሰውን የማኅበረ ቅዱሳንን አመራርና አባላት በአክራሪነት የሚከስ ነው የተባለ ዶክመንተሪ ፊልም ለማዘጋጀት መታቀዱ ተጠቆመ፡፡ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ አንዳንድ ሓላፊዎች አቀብለውታል በተባለ መረጃ እንደሚታገዝና በመንግሥት አካል እንደሚሰናዳ የተገለጸው የዶክመንተሪ ዝግጅቱ በማኅበሩ ኻያ አመራሮች እና አባላት ላይ እንዳነጣጠረ ተገልጧል፡፡

Sunday 16 February 2014

የቤተክህነቱ የእግድ "ቀጭን" ትእዛዝ ምን ያመለክተናል?

ከመለሰ ዘነበወርቅ

በዚህ ሳምንት ማህበረ ቅዱሳን ከ200 በላይ የአብነት ት/ቤቶች መምህራንን ከተለያዩ የሃገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ጋር በመሆን በችግሮቻቸው ዙሪያ እንዲሁም ለቤተክርስቲያን በሚያበረክቱት ግልጋሎት ላይ ለመምከር ያዘጋጀውን ጉባኤ ከፓትሪያርክ አቡነ ማትያስ በተላከች አንዲት ደብዳቤ ሊታገድ ችሏል። ለመሆኑ ይህ እግድ ምን ይነግረናል?

Saturday 15 February 2014

ማኅበረ ቅዱሳን ከ 200 በላይ የአብነት መምህራን የምክክር ስብሰባ መታገድ ላይ ለአብነት መምህራኑ ገለጻ ሰጠ

ጉባኤው በ "አባ" ሰረቀብርሃን ምክንያት በመጨረሻው ሰአታት ላይ እንዲቋረጥ ተደርጓል። በጉባኤው ላይ የተጋበዙ የአለም ባንክ በኢትዮጵያ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ትልልቅ ባለስልጣናት ሃዘናቸውን ገልጸዋል። ለጉባኤው መሳካት ማህበሩ ብዙ ሺህ ብር ወጪ እንዳወጣበት አሳውቋል። ማህበሩ ለእዲህ ያሉ ችግሮች አዲስ እንዳልሆነና የሚጠበቅ እንደነበረም መ/ር ብርሃኑ አድማስ ተናግረዋል። "ይህ ጉባኤ በአይነቱ የተለየ ሰለሆነ፣ በቤተክህነቱም በዓመቱ መጀመሪያ ላይ አሳውቀን ተቀባይነትን ስላገኘ እንዲሁም ከተለያየ መስሪያ ቤቶች የተጋበዙ ታታላቅ ባለስልጣናትም ስለሚገኙ ነበር እክል አያጋጥመውም ብለን የተዘናጋነው። ሆኖም እግዚአብሄር ፈቅዶ ይህ ከሆነ መልካም ነው" መ/ር ብርሃኑ አድማስ። 

በጉባኤው ላይ የተገኙት አባቶችም ሃዘናቸውን ትህትና በተሞላበት መንገድ ገልጸዋል። ቅዱስ ፓትሪያርኩንም ማነጋገር እንደሚፈልጉ ተናግረዋል። ሆኖም ግን ሁሉም አባቶች ብጹህ ፓትሪያርኩን ማነጋገር ባይችሉም ጥቂት የተመረጡ መምህራን ግን እንዲያነጋግሩ ተፈቅዶላቸዋል። ቅዱስ ፓትሪያርኩም "መመሪያ መመሪያ ነው!" የሚል ምላሽ እንደሰጧቸው መምህራኑ ተናግረዋል።

ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ በመጫን ማድመጥ ይችላሉ!
http://www.dtradio.org/index.php?option=com_content&amp%3Bview=article&amp%3Bid=136%3A-7-2006-february-14-2014-&amp%3Bcatid=1%3Aweekly-tansmission#.Uv6ECtKvl3w.facebook

Tuesday 11 February 2014

የዘመናችን የአርዮሳውያን ግብር

ኦልማን የተባለ የታሪክ ፀሃፊ በ379 በቁስጥንጥንያ የነበረውን የሃይማኖት ሁኔታ እንደሚከተለው ገልፆታል፡፡

Sunday 9 February 2014

ከ2000 ዓመት በኋላ እንደ አዲስ እንመዘገባለን፣ እንደ አዲስም እንታወቃለን

ሰሞኑን የፌድራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሃይማኖት ተቋማትን ለመመዝገብ የወጣ ረቂቅ መመሪያ› የሚል ወረቀት አስተያየት ይሰጥበት ዘንድ ለእምነት ተቋማት አሠራጭቷል፡፡ ይህ መመርያ የያዛቸውን ጉዳዮች እያንዳንዳቸውን እየነጠሉ መመልከት ያስፈልጋል፡፡ ይህንንም ወደፊት የምናደርገው ይሆናል፡፡ ለአሁኑ ግን መመሪያውን ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ነባራዊ፣ ሉዓላዊና መንፈሳዊ ጠባያት ጋር በማዛመድ ብቻ እንመለከተዋለን፡፡

1. መመሪያው የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዩ ሁኔታ ከግምት ያላስገባ ነው
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላለፉት 2000 ዓመታት በምድሪቱ ላይ የኖረች፣ የሰበከች ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ ክፉውንም ሆነ ደጉንም እኩል የቀመሰች፣ እንዲያውም የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በመሆንዋ ብቻ ልዩ ጉዳት የደረሰባትም ናት፡፡ በጣልያን ወረራ ጊዜ የተሠውትን ጳጳሳትና መነኮሳት ማሰቡ ብቻ ለዚህ የቅርብ ምሳሌ ነው፡፡ ይህቺ ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ሂደት ውስጥ በሀገሪቱ ሃይማኖታዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ውስጥ ልዩ የሆነና የማይተካ ሚና ተጫውታለች፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ተመሥርታ ሀገሪቱንም መሥርታለች፡፡

ይህንን ሁሉ ዘንግቶ በ2005 ዓም ላይ ቤተ ክርስቲያኒቱን እንደ አዲስ ተመዝገቢ፣ እንደ አዲስ ፈቃድ አውጭ፣ እንደ አዲስ ደንብና መመሪያሽን አምጭ ማለት እጅግ አሳዛኝም አስገራሚም ነገር ነው፡፡ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱም ራሱ ከፈለገ መረጃ ሰብስቦ መመዝገብና ማወቅ ነበረበት እንጂ ሰነድ አምጭ፣ ደንብ አስገቢ፣ ፈቃድ አውጭና ልወቅሽ ማለት አልነበረበትም፡፡

Friday 7 February 2014

"እግዚኦ አርእየኒ እመከ = አቤቱ እናትህን አሳየኝ"

በቴዎድሮስ በለጠ

"ሰባኪው" በአትሮንሱ ላይ "ቆሟል" .......የቆመበትን እንኳ አያውቅ ( ሊቁ ድንግልን አትሮንሱ ለቃለ አብ ይላታልና...)

ምዕመናን ይጠይቃሉ " ስለ ድንግል ማርያም አስተምረን" ?
ጥያቄውን "ይመልስባቸዋል" እንዲህ ሲል "እኛ እዚህ ድረስ የመጣነው ጌታን ልንሰብክላችሁ እንጂ ስለ ማርያም ልናወራላችሁ አይደለም.... እስኪ ቅዱስ ጳውሎስን ተመልከቱ ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ ስለ ሶምሶንም ስለ ዮፍታሔም""""እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛል አለ እሱ ጊዜ ያለው ስለ ጌታ ብቻ ለመመስከር ነው...."
ይህ በአይሁድ ምኩራብ ፥ በተንባላት አውድ አልያም በመናፍቃን አዳራሽ የተነገረ እንዳይመስላችሁ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን መድረክ ላይ በድፍረት የተፈጸመ እንጂ :: እውነትም ሥፍራው የምሕረት አደባባይ ነው አምላክ ለቁጣና ለመአት የቅጣት ሠይፉን የሚያዘገይበት ለትዕግስትና ለይቅርታ የፍቅር እጁን የሚዘረጋበት "አውደ ምሕረት"! .... እንግዲህ ምን እንላለን "እግዚኦ ተዘከራ ለአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ሀለወት እምጽንፍ እስከ አጽናፈ ዓለም" 

Monday 3 February 2014

ኢትዮጵያ 46

በሳህሉ ወንድወሰን

ይህ ጽሁፍ አቶ ሳህሉ ወንድወሰን በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ያሰፈሩትን እንዳለ በመውሰድና ጥቂት ያልተካተቱትንም በመጨመር የተዘጋጀ ነው።

ኢትዮጵያ በመጽሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ ምን ያክል ጊዜ መነሳቷንና የት የት ቦታ ላይ እንደተጠቀሰችም ማሳያ ነው። ለወንድማችን ቃለህይወትን ያሰማልን።
መልካም ንባብ!




ንዋያተ ቅዱሳቱ የማን ናቸው?

ጥር 26 ቀን 2006 ዓ.ም.
ምንጭ፡- ሐመር መጽሔት 21ኛ ዓመት ቁጥር 8 2006 ዓ.ም.


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዜማ መሣሪያዎች ከቅዱስ ያሬድ ጀምሮ በርካታ ሊቃውንት ሲያገለግሉበት የነበረና የሰማያዊውን የዝማሬ ሥርዓት መነሻ ያደረገ፣ ሰማያዊውንም ዓለም የሚያሳስብ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃልም መነሻ ተደርጎ የተመረጠ፣ ኢትዮጵያዊ መልክ ኖሯቸውም የተዘጋጁ ናቸው፡፡

እነዚህ የዜማ መሣሪያዎች ቤተክርስቲያናችን ይዛ በምትጠቀምበት ቅርጽና ይዘት የሚገኙት በኢትዮጵያና ኢትጵያውያን እጅ ብቻ ነው፡፡ ይልቁንም ደግሞ የአንድ ቤተ ሃይማኖት ማለትም የኦርቶዶክስ ሃይማኖት መጠቀሚያ ሆነው እያገለገሉ ያሉ ናቸው፡፡

ይህ በእንዲህ እያለ ግን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ሌሎች ቤተእምነቶች በከበሮ፣ በመቋሚያና ጸናጽሉ በራሳቸው ተጠቅመው በራሳቸው መንገድ የራሳቸውን እምነት ሲያራምዱበት እየታየ ነው፡፡ በመድረኮቻቸው ያንን ሲያደርጉ ታይተዋል፡፡ በቴሌቪዥን ፕሮግራም ሲያስተላልፉ ተስተውሏል፡፡

በተመሳሳይ ዜማው የዝማሬ ሥርዓቱ የበዓላት ሥርዓቱ ንዋየ ቅድሳቱ ሁሉ ደረጃ በደረጃ በተለያዩ ቤተእምነቶች ቁጥጥር ሥር ወድቋል፡፡ የበዓላት ቀናቱ ጭምር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ባሕረ ሐሳብ መሠረት የሚወጣ ቢሆንም እንደራሳቸው አደርገው በዓል ሲያደርጓቸው ልዩ ልዩ መርኀ ግብር ሲፈጸምባቸው ይታያል፡፡ ለዚህ ማሳያ የሚሆነው የመስቀል በዓል ነው፡፡ በዓለ መስቀል ኦርቶዶክሳውያንን ብቻ የሚመለከት በዓል ቢሆንም አሁን ግን በቤተክርስቲያኒቱ የበዓል ዐውድ ውስጥ ሌሎች ቤተእምነቶች የራሳቸውም እንደሆነ በሚያስመስል መንገድ ስለሚቀርቡ ግራ መጋባት እየፈጠረ ነው፡፡ ይሄ ነገር በዚሁ ከቀጠለ ቤተክርስቲያናችን የእኔ የምትለው የራሷ ነገር እየጠፋ ሊመጣ ይችላል፡፡

Monday 27 January 2014

የሆሳዕና ቡሻና በዐታ ለማርያም ገዳም ተቃጠለ

በእንዳለ ደምስስበሐድያና ስልጢ ሀገረ ስብከት ጎረጎራ ወረዳ ውቅሮ ፋለታ ቀበሌ የደብረ ምጥማቅ ሻና በዓታ ለማርያም ገዳም ጥር 10 ቀን 2006 ዓ.ም. የከተራ ዕለት መነሻው ባልተወቀ ምክንያት ሙሉ ለሙሉ መቃጠሉን የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ቢኒያም መንቻሮ ገለጹ፡፡



ሥራ አስኪያጁ በሰጡን መረጃም የከተራ ዕለት የበዐታ ለማርያም ታቦት ወደ ጥምቀተ ባሕር ከወረደ በኋላ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ መቃጠሉን ገልጸው ቤተ ክርስቲያኑ ንዋያተ ቅዱሳቱን ጨምሮ ሙሉ ለሙሉ ወድሟል ብለዋል፡፡

በካዝና ውሰጥ የነበረው የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጽላት ካዝናው በእሳቱ በከፍተኛ ሁኔታ በመለብለቡ ምክንያት መክፈት እንዳልተቻለና መቃጠልና አለመቃጠሉን እንዳልተረጋገጠ ያስታወቁት ሥራ አስኪያጁ፤ ጉዳዩን ለፖሊስ በማሳወቅ የቃጠሎውን መንስኤ ለማጥራት ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

የቡሻና በዐታ ለማርያም ገዳም ከዚህ በፊት ሥዕለ አድኅኖ በዛፎች ላይ ታይቶበት በነበረ ቦታ መቃኞ ተሰርቶለት ሐምሌ 2001 ዓ.ም. ቅዳሴ ቤቱ እንደተከበረ ይታወቃል፡፡

የቋሚ ሲኖዶሱን ውሳኔ የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ሻረው!


በርካታ ሚልዮን የምእመናን ገንዘብ የተመዘበረበት የድሬዳዋ ቅ/ገብርኤል ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ግንባታና ሒሳብ በብቁ እና ገለልተኛ ባለሞያዎች እንዲመረመር ቅ/ሲኖዶሱ ያስተላለፈውን ውሳኔ ልዩ ጽ/ቤቱ እንዲዘገይ አዘዘ – በውል ከተያዘው ገንዘብ ውጭ ከ8 ሚልዮን በላይ ብር የወጣበትና ሥራው ሳይጠናቀቅ በ6 ዓመት የዘገየው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ግድግዳ ተሰነጣጥቋል፤ ዋናው መካከለኛ ጉልላት እንዳይወድቅ ያሰጋል

‹‹ብፁዕ አባታችን፣ በድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅ/ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እየተፈጸመ የሚገኘው ከባድ ወንጀል ሕዝበ ክርስቲያኑን እያስቆጣ ከመምጣቱም ባሻገር ብፁዕ አባታችን ይህን እየሰሙና እያወቁ ምነው ዝም አሉ ብሎ ሕዝቡ እንዲያስብ አድርጎታል፡፡… የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ጅምር ሥራ አልቆ ማየት እንፈልጋለን፡፡ የደብሩ ሕንፃ አሠሪ ኮሚቴ በአስቸኳይ ሕዝቡ በሚመርጣቸው የኮሚቴ አባላት ይተካልን፡፡ ይህ የማይደረግ ከኾነና ኹኔታው ባለበት ከቀጠለ ለሚፈጠረው ችግር ሓላፊነቱን የማንወስድ መኾኑን እናሳውቃለን፡፡›› /የደብሩን ወቅታዊ ጉዳይ ለማሳወቅ ምእመናኑ በኅዳር ፳፻፬ ዓ.ም. ለብፁዕ አቡነ ገሪማ ከጻፉት አቤቱታ የተወሰደ/

Sunday 26 January 2014

በዐረቡ ምድር የመጀመሪያዋ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ልትታነጽ ነው

ከዳንኤል ክብረት የፌስቡክ ገጽ ላይ የተወሰደ


በመካከለኛው ምሥራቅ ከእሥራኤል ቀጥሎ ሁለተኛዋ፣ በዐረቡ ምድር ደግሞ የመጀመሪያዋ የምትሆነው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በኳታር ምድር ልትታነጽ ነው፡፡

Friday 24 January 2014

ፓትርያርኩ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በሙስና ላይ እንዲዘምቱ አዘዙ

  • በቤተ ክርስቲያናችን ሸፍጥና ጉቦ ተንሰራፍቷል›› /ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ/
  • ሰንበት ት/ቤቶቹ የአማሳኝ አስተዳዳሪዎችን ዶሴ ለፓትርያርኩ ለማቅረብ ተዘጋጅተዋል
(አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፫ ቁጥር ፯፻፴፩፤ ቅዳሜ ጥር ፲ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.)
His Holiness Patriartch Abune Mathias
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ በተንሰራፋውና ለዕድገቷ መሰናክል ኾኖ በተደነቀረው ሙስናና ሸፍጥ ላይ በተጠናከረ ኃይል በመዝመት የተጀመረውን የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ከዳር እንዲያደርሱ አዘዙ፡፡

ፓትርያርኩ: የቤተ ክርስቲያኒቷ የመዋቅር ለውጥ ሕግ ረቂቅ ‹‹የእኔ ጩኸት ነው›› አሉ

ለአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ የሚሰማው የካህናቱና ምእመናኑ ጩኸት በርክቷል

(ፋክት መጽሔት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፳፱ ጥር ፳፻፮ ዓ.ም.)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአስተዳደራዊ መዋቅሯ ትክክለኛውን መሥመር ይዛ ወደ ቀደመ የቅድስናና ንጽሕና ክብሯ እንድትመለስ በአደረጃጀትዋና አሠራሯ ላይ እየተካሔደ የሚገኘው የተቋማዊ ለውጥ ጥናት፣ ‹‹ከጅምሩም የእኔ ጩኸት ነው፤ የእኔ አጀንዳ ነው፤ ዛሬ ከደረሰበትም ወደ ኋላ አይመለስም፤›› ሲሉ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ቃል ገቡ፡፡

ፓትርያርኩ ይህን የተናገሩት፣ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናት ሳይዘገይ ተግባራዊ እንዲኾን ጥያቄ ያቀረቡ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችን፣ የጽ/ቤት ሠራተኞችን፣ ካህናትን፣ መምህራንና ምእመናንን ጥር 2ና 5 ቀን 2006 ዓ.ም. በጽ/ቤታቸውና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው፡፡

Monday 13 January 2014

አርባ አራቱ ታቦት የሚለው ታሪክ መነሻው ምንድን ነው ?

እውን ታቦት አርባ አራት ብቻ ? 
(ከኦርቶዶክስ እና መጽሃፍ ቅዱስ)

መግቢያ ጎንደር በኢትዮጵያ የመንግሥት ታሪክ ከአክሱምና ላሊበላ ቀጥሎ ትልቋ የመንግሥት ማዕከል ነበረች፡፡ በመንግሥት ማዕከልነት የተቆረቆረችው በአፄ ፋሲል (1624-1660 ዓ.ም) ነው፡፡ ጎንደር የመንግሥት ማዕከል ብቻ ሳትሆን በጊዜው የመንፈሳዊ ትምህርት ማዕከልም ነበረች፡፡ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የመጻሕፍት እና የአቋቋም ትምህርት ይበልጥ የተስፋፋውና በየሀገሩ ያሉ ሊቃውንት በመናገሻ ከተማዋ ጎንደር በነገሥታቱ አማካይነት በመሰባሰባቸው ሲሆን ከዚያን ዘመን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ መንፈሳዊ ትምህርት በስፋት የሚሰጥባት የትምህርት ማዕከል ለመሆን ችላለች፡፡

Thursday 9 January 2014

ሰበር ዜና – ተቃዋሚ ነኝ ባዩ የእነኃይሌ ኣብርሃ ቡድን ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን ይቅርታ ጠየቀ

ተቃዋሚ ነኝ ባዩ የእነኃይሌ ኣብርሃ ቡድን ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን ይቅርታ ጠየቀ፤ ‹ተቃውሞው›÷ የቡድኑ መሪዎች አላግባብ ባካበቱት ሀብት በሕግ ላለመጠየቅ በመከላከያነት የጀመሩት መኾኑን ለሊቀ ጳጳሱ አምነዋል፤ ይቅርታው የሙሰኞች ሽፋን እንዳይኾን የሚያስጠነቅቁ የተቋማዊ ለውጥ ኃይሎች የአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱን በመደገፍ ነገ ዐርብ ፓትርያርኩን ለማነጋገር የሚያደርጉትን ዝግጅት አጠናክረው ቀጥለዋል


ተቃዋሚ ነኝ ባዩ ቡድን ይቅርታ ለመጠየቅ የተገደደው፣ የቡድኑ ሰብሳቢ የኾኑት የኮተቤ ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሊቀ ትጉሃን ዘካርያስ ሐዲስ ‹‹ተቃውሟችን ከመዋቅር ጥናቱ እንጂ አቡነ እስጢፋኖስ ይነሡልን የሚል ጥያቄ የእኛ አይደለም›› በሚል ታኅሣሥ ፳፫ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. በፓትርያርኩና በስምንት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፊት በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ላይ በተሰነዘረው መሠረተ ቢስ ውንጀላ ባለመስማማት ከኹሉ ቀድመው ሊቀ ጳጳሱን ይቅርታ መጠየቃቸው በቡድኑ አባላት መካከል የፈጠረው መከፋፈል ነው፡፡

‹‹የዘካርያስ እናት ሞተው ለልቅሶ ራያ በነበርንበት ወቅት የሀ/ስብከቱ አንዳንድ የመምሪያ ሓላፊዎች [የለውጡ ደጋፊ መስሎ በርካታ አሻጥሮችን የሚፈጽመው አደገኛው ጉቦኛ የሒሳብና በጀት ዋና ክፍል ሓላፊ ሊቀ ጠበብት ኤልያስ ተጫነ] ደውለው÷ አቡነ እስጢፋኖስ አንተን ለመክሠሥ ከመዝገብ ቤት ሰነድ እያወጡብኽ ነው፤ ኃጢአት እየተፈለገብኽ ነው፤ ወኅኒ ሊከቱኽ ነው ስለተባልኹ በአልሞት ባይ ተጋዳይነት ስሜት የተናገርኹት ነው፤ የጠላ ሰው ብዙ ይናገራል፤ ብፁዕነትዎ አስቀይሜዎታለኹ፤ ለአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የሚመጥን ከእርስዎ የተሻለ ሊቀ ጳጳስ ከየት ይመጣል? በልጅነት የተናገርኹት ነው፤ የአባትነትዎ ይቅርታ ይደረግልኝ፡፡›› /የተቃዋሚ ነኝ ባዩ ቡድን መሪ ኃይሌ ኣብርሃ በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ጫማ ላይ ወድቆ ከተናዘዘው/
የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ‹‹ከሓላፊነታቸው ይነሡ፤ ከሲኖዶስ አባልነት ይሰረዙ›› የሚለው ጥያቄ ኃይሌ ኣብርሃ ከምክራቸው ውጭ ያቀረበው መኾኑን በመጥቀስ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ እና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፊት ስለተናገረው የድፍረት ቃል በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ እግር ላይ ወድቀው ይቅርታ የጠየቁት የቡድኑ መሪዎች፣ የሀ/ስብከቱን የአደረጃጀትና አሠራር ጥናት መቃወማችንን ግን እንቀጥላለን ብለዋል፡፡

የ‹ተቃውሟቸው› ትኩረት ጥናቱን ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን መሥራቱና በጥቂት አንቀጾች ላይ ብቻ የተወሰነ›› መኾኑን የተናገሩት የቡድኑ መሪዎች፣ ከፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አቀንቃኝነታቸው አኳያ ጥያቄዎቻቸውን እየለጠጡ ሽፋን የሚሰጡላቸውን ብሎጎች ‹‹የመናፍቃን›› ሲሉ ገልጸዋቸዋል፡፡ በሕገ ወጥ መንገድ ባካበቱት ሀብትና በከባድ እምነት ማጉደል በሕግ የመጠየቅ፣ በሰነዘሩት መሠረተ ቢስ ውንጀላ ደግሞ ሥነ ምግባራዊ ርምጃ ይጠብቃቸዋል የተባሉት የተቃዋሚ ነኝ ባይ ቡድኑ ቀንደኛ መሪዎች፣ በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ጫማ ላይ ወድቀው ይቅርታ መጠየቃቸው በእብሪታቸው ላሞገሷቸው አቡነ ሳዊሮስና የተቋማዊ ለውጥ አመራር ንቅናቄውን በጠዋት ጤዛ ለመሰሉት የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አቀንቃኝ ብሎጎች ታላቅ ኀፍረትና መቅሰፍት ነው፡፡
የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ ለውይይት እንዲቀርብ ሲወስን ሰነዱ እንዲተች በመኾኑ ድጋፍ ይኹን ተቃውሞ የሚጠበቅና መብትም መኾኑን የተናገሩት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፣ ቡድኑ ተቃውሞውን በስሜታዊነትና መዋቅሩን ሳይከተል ያቀረበበት መንገድ ተቀባይነት እንደሌለው በመግለጽ በጥናቱ ይዘት ላይ ብቻ የተመሠረተ ትችቱን ደረጃውን በጠበቀና በተደራጀ መንገድ እንዲያቀርብ አሳስበውታል፤ በምትኩ ከሁለት ሚልዮን በላይ የሀ/ስብከቱ ካህናትና ምእመናን ተወካዮች ከፍተኛ ድጋፋቸውን ያረጋገጡለትን ጥናት በማኅበረ ቅዱሳን እያሳበቡ እቃወማለኹ ማለት እንደማያዋጣቸው መክረዋቸዋል፤ በአባትነታቸው ግን የይቅርታ ጥያቄውን መቀበላቸውንና ይቅርታ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡

የቡድኑ መሪዎች መዋቅሩን ባልተከተለ የተቃውሞ አቀራረባቸውና በዐመፅ በተሞላ ዘለፋቸው ከሚከተላቸው የከፋ ቅጣት ይልቅ ይቅርታ እንዲጠይቁ አግባብቻለኹ የሚለው አሸማጋይ አካል አንዳንድ አባላት (በስም ለይቶ መጥቀስ ይቻላል)÷ነገ፣ ጥር ፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. በ9፡00 የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የሰበካ ጉባኤያት ምክትል ሊቃነ መናብርት፣ ካህናትና የአብነት መምህራን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጋራ የተያዘላቸውን የድጋፍ መግለጫ ስብሰባ መርሐ ግብር በ‹‹ይቅርታ ተጠይቋል›› ሰበብ የማኮላሸት ዓላማ እንዳላቸው ተጋልጧል፡፡ በስም ተለይተው የተጠቀሱት እኒህ ሦስት የአሸማጋይ አካሉ አባላት በተቋማዊ ለውጥ ተነቃናቂ ኃይሎች የጥንቃቄ ክትትል እየተደረገባቸው ነው፡፡

* * *

የፓትርያርኩ አማካሪ በሚል ይፋ ባልተደረገ የሥራ ድርሻ የፓትርያርኩን ልዩ ጽ/ቤት በቅርበት እንደሚቆጣጠሩ የሚነገርላቸው ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ የተቃዋሚ ነኝ ባይ ቡድኑን በኅቡእ የሚያስተባብሩ እንደኾኑ ከቡድኑ አፈንግጠው የወጡ አባላት አጋልጠዋል፡፡ ንቡረ እዱ፣ አባላቱ የቻሉትን ያህል አስተዳዳሪዎች፣ ካህናትና ሠራተኞች ቀስቅሰው እንዲያሰልፉ እንዳግባቧቸው የሚናገሩት እኒህ ወገኖች፣ ንቡረ እዱ የሚያስተባብሩት እንቅስቃሴ ዓላማ ‹‹ተቋማዊ ለውጡን በመቃወም አድርጎ ማኅበረ ቅዱሳንን በማጋለጥ በመንግሥት ማስመታት፤ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን ከሓላፊነታቸው ማስነሣት፣ አንድ ባራኪ ጳጳስ (አቡነ ሳዊሮስ?) ብቻ አስቀምጦ ሀ/ስብከቱን መቆጣጠር›› መኾኑን አስረድተዋል፡፡

ንቡረ እዱ ከፍተኛ ሚና እንደተጫወቱበት የተነገረውና በፓትርያርኩ የስም ዝርዝር አቅራቢነት ቋሚ ሲኖዶስ ወስኖ አቋቁሞታል የተባለው ‹‹የሊቃውንት ጉባኤ››÷ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን የአደረጃጀትና አሠራር ሰነድ ለመገምገም ያለው የሕግ ተቀባይነትና ሞያዊ አግባብነት የጥቅምት ቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ካሳለፈው ውሳኔ አንጻር እየተጤነ ነው፡፡
በብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ ሰብሳቢነት የሚመራውና ዘጠኝ አባላት አሉት በተባለው ‹‹ሊቃውንት ጉባኤ›› ተካተው የነበሩት መልአከ ታቦር ተሾመ ዘሪሁንና ሊቀ ካህናት ብርሃኑ ገብረ ዐማኑኤል ‹‹ማኅበረ ቅዱሳኖች ናቸው›› በሚል እንዲወጡ ተደርጎ በምትካቸው እነአባ ሰረቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኤል መተካታቸው፣ በይቀጥላልም እነኃይሌ ኣብርሃ መላውን ገዳማትና አድባራት ሳያወያዩ መርጠናቸዋል ያሏቸውን ወኪሎች በሊቅነት ስም ለማስረግ መዘጋጀታቸው‹‹ሊቃውንት ጉባኤ›› የማቋቋሙን ዓላማና ቅንነት አጠያያቂ አድርጎታል፡፡

የጥቅምት ቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ያሳለፈው ውሳኔ፣ የአደረጃጀትና አሠራር ሰነዱ ‹‹ወደታች ወርዶ በካህናት፣ በምእመናንና በሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በውይይት ዳብሮ በሚገባ ተጠንቶና ተስተካክሎ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲቀርብና ቋሚ ሲኖዶሱም ዓይቶና ተመልክቶ በሥራ ላይ እንዲያውል›› በመኾኑ፣ ከዚህ በኋላ የሚጠበቀው 2700 የገዳማትና አድባራት ልኡካን የተወያዩበትና 96 በመቶ ድጋፋቸውን ያረጋገጠውን ጥናት በተሰበሰበው ግብዓት አጠናክሮ ለቋሚ ሲኖዶሱ በማቅረብ አጽድቆ የትግበራ ዕቅድ ወደሚወጣበት ምዕራፍ መግባት ብቻ ነው፡፡

የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለጥናቱ በሰጠው ይኹንታና የአፈጻጸም አቅጣጫ መሠረት ጥናቱን እንዲተገብር የማድረግ ውክልና የተላለፈለት ቋሚ ሲኖዶስ በውሳኔው መሠረት የተጣለበትን ከፍ ያለ አደራ በመወጣት የእነንቡረ እድ ኤልያስን መሠሪ ዓላማ እንደሚያከሽፍና የቤተ ክህነታችንን ተቋማዊ ለውጥ ውጥን እውን እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡

* * *
በይቅርታ ሥነ ሥርዐቱ ላይ መልአከ ገነት ኃይሌ ኣብርሃ (ፊት መልአከ መንክራት) በበርካታ ሚልዮን ብር ጉድለት ከሚጠየቁበት የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እልቅና መነሣታቸው አግባብ እንዳልነበር መናገራቸው ከስሕተታቸው ለመታረም እንዳልተዘጋጁ አመልካች ኾኗል፡፡ ከኦጋዴን እስከ አዲስ አበባ በአያሌ የምግባርና የሙስና ቅሌቶች የሚታወቁት ሊቀ ትጉሃን ዘካርያስ ሐዲስ ደግሞ የአዲስ አበባው አልበቃ ብሏቸው ድሬዳዋ ሀ/ስብከት ድረስ እየደወሉ ‹‹ተነሡ! ለውጡ ወደ እናንተም ሊመጣ ነው›› በሚል የአድባራት አለቆችንና የአስተዳደር ሠራተኞችን ለማነሣሣት እየሠሩ መኾኑ ተጠቁሟል፡፡
ተቃዋሚ ነኝ ባይ ቡድኑ በፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ላይ የተነሣው የ‹‹ዘወር አድርጓቸው›› ጥያቄ የማይወክለው መኾኑንና በአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ ላይ ግን ‹ተቃውሞውን› እንደሚቀጥል ቢያረጋግጥም በውስጡ ግን ጥያቄያቸውን ‹‹ከቤተ ክህነቱ መዋቅር ውጭ ለመንግሥት ማቅረብ አለብን›› የሚል አቋም የሚያራምዱ፣ እንደ ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ተክለ ጊዮርጊስ ያሉ ግለሰቦች ይገኙበታል፡፡

እነሊቀ ትጉሃን ዘካርያስ ሐዲስንና መልአከ ገነት ኃይሌ ኣብርሃን ‹‹ጃኬት ለባሾች›› እያሉ የሚያጣጥሏቸውና እንደማይመጥኗቸው የሚናገሩት እነሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ በቡድኑ ውስጥ መነኮሳት አስተዳዳሪዎች ባለመካተታቸው መከፋታቸውንና ከእናንተ ጋራ አልሳተፍም በሚል ሌላ አንጃ ለመፍጠር እየሞከሩ መኾኑም ተጠቁሟል – ‹‹ወደ መንግሥት የምትሰለፉ ከኾነ ንገሩኝ፤ እሔዳለኹ፡፡››

የሀ/ስብከቱን የአደረጃጀትና አሠራር ጥናት ያካሔደውን የባለሞያ ቡድን (በእነርሱ አነጋገር የአንኮበርን ሥርዐት ለመመለስ የሚሠራውን ማኅበረ ቅዱሳንን) በትጥቅ በተደገፈ የኃይል ርምጃ በሀ/ስብከቱ ከተሰጠው ቢሮ አስለቅቃለኹ፤ ለዚኽም እስከ አፍንጫዬ ታጥቄአለኹ፤ ካስፈለገም በረሓውን ዐውቀዋለኹ እያለ ፓትርያርኩንና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱን ለማሸማቀቅ ሲሞክር የሰነበተው ተቃዋሚ ነኝ ባይ ቡድኑ በዋናነት አምስት ሙሰኛና ጎጠኛ የአድባራት አስተዳዳሪዎችየሚመሩት ነው፡፡
አስተዳዳሪዎቹን በመናጆነት የተባበሯቸውና በቁጥር ከ110 የማይበልጡት ተሰላፊዎችም ጥቂት ጸሐፊዎችና ሒሳብ ሹሞች በሥራ ዋስትናቸው ያስፈራሯቸው የጥበቃና ጽዳት ሠራተኞች፣ ሀ/ስብከቱ ያጸደቀውን የደመወዝ ጭማሪ አንከፍላችኹም እያሉ ያስገደዷቸው አገልጋዮች፣ በለመዱት የድለላ ሰንሰለት እናስቀጥራችኋለን እያሉ ተስፋ የሰጧቸው ሙዳየ ምጽዋት አዟሪዎችና ደጅ ጠኚዎች ብቻ መኾናቸው ተረጋግጧል፡፡

መነባንብ በአርቲስት ሽመልስ አበራ "ጆሮ ያለህ ስማ"


Wednesday 8 January 2014

EOTC Television

ዝማሬ (በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን እና በዲ/ን ቴዎድሮስ) እና ትምሕርት በመጋቢ ሃዲስ እሸቱ አለማየሁ

ለክርስቲያን ጎሳው ማነው?

ከመብራቱ ጌታቸው

ከፌስቡክ ገጽ ላይ የተወሰደ

ለክርስቲያን ጎሳው ማነው? ዘሩስ ከወዴት ነው? ወገንተኝነቱስ ለየትኛው ብሔር ነው? አለም በዲያቢሎስ ሃሳብ ታነክሳለች ፡ በክርስቶስ ሃሳብ ግን ትፀናለች ፤ አለም በዲያቢሎስ ወሬ ትከፈላለች ፡ በክርስቶስ ግን አንድ ትሆናለች።

"ዘርህ ማነው?" ይሉኛል ፡ እኔ ግን የክርስቲያን ዘሩ ምንድን ነው? እላቸዋለሁ፡፡ "አማራ ነህ ?" ይሉኛል ፡ አዋ አማራ ወገኔ ነው እላቸዋለሁ። 

ሰበር - ዜና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ጳጳስ አቡነ ሳዊሮስ እና ሥራስኪያጃቸው አባ አፈወርቅ በአስቸኳይ ከሀገረ ስብከታችን እንዲነሱ ሲሉ ምእመናን ጠየቁ


• በእኛ ዘመን አንዲህ ያለ አባት ገጥሞን አያወቅም/ የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች /
• ታላቁ ሐዋርያ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዲዮስቆሮስ በነበሩበት ፤ባስተማሩበት ፤ሕሙማነ ሥጋ ወነፍስን በፈወሱበት ሀገረ ስብከት እንዲህ ያሉ አባት በመመደባቸው እናዝናለን/ ካህናትና ምእመናን/
• የህዝቡን ጥያቄ በማኅበረ ቅዱሳን ማሳበብ ህዝቡን መናቅ ነው/ምእመናን/

Saturday 4 January 2014

ሰበር ዜና ነገ እሑድ በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን የሀ/ስብከቱን የተቋማዊ ለውጥ ጥናት በመደገፍ በ8፡00 ወደ መንበረ ፓትርያርኩ ሊተሙ ነው

የአ/አ ገዳማትና አድባራት ሰበካ ጉባኤያት ሊቃነ መናብርት፣ ካህናት፣ ሰንበት ት/ቤቶችና ምእመናን የሀ/ስብከቱን የተቋማዊ ለውጥ ጥናት በመደገፍ ነገ እሑድ በ8፡00 ወደ መንበረ ፓትርያርኩ በሺዎች ሊተሙ ነው፤ የአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ ጸድቆ እንዲተገበርና የሙሰኛ አስተዳዳሪዎችና ተቃዋሚ ነን ባዮች የሀብት ምንጭ እንዲመረመር ይጠይቃሉ

‹‹ምእመናን የቤተ ክርስቲያን አባላት እንጂ አካላት አይደሉም›› ባዮቹና በተቃውሟቸው ‹‹መንግሥት እየደገፈን ነው›› ያሉት እነኃይሌ ኣብርሃ÷ ፓትርያርኩ ረዳታቸውን ‹‹እስከ ገና ድረስ ዘወር የማያደርጉ›› ከኾነ እንቅስቃሴያቸው ትጥቃዊ መልክ እንደሚኖረው በማስጠንቀቅ ዝተዋል። በተጨማሪም የሚከተለውን የማስፈራሪያ ዛቻ መሳይ መልእክት ለማስተላለፍ ሞክረዋል – ‹‹ያኹኑ ሊቀ ጳጳስ የማን ረዳት ናቸው፤ የማኅበረ ቅዱሳን ናቸው ወይስ የቅዱስነትዎ? በሊቀ ጳጳሱ ፈረጅያ ሥር ተከተው ጀግና ሊቀ ጳጳስ በሠራው ሀ/ስብከት ቢሮ ተሰጥቷቸው እያረቀቁበት ስለኾነ እንዲወጡ ይደረግልን! ከአቅማችኹ በላይ ከኾነ አሳልፋችኹ ለመንግሥት ስጡ፤ ሄደን እኛ እናስለቅቀዋለን፤ ውጊያ ከመገባቱ በፊት ወረቀቱ ተቀዶ መመለስ አለበት፤ እነንቡረ እድ ኤልያስ እነአባ ሰረቀ ያርቅቁ፡፡ ታኅሣሥ ገና ላይ ረዳት ሊቀ ጳጳሱ ወደ ጅማቸው ብቻ ቢሄዱ፤ ይህን ከተማ አበጣብጠውታል፤ መንግሥትም ስለማይናገር ነው እንጂ እያዘነ ነው፤ ረዳትዎን ዘወር ያድርጉልን!››

በተጨማሪም በግፍና ነውር በተሞላው አስተዳደራቸው የተነሣ የወሊሶ ካህናትና ምእመናን ያባረሯቸው አቡነ ሳዊሮስ የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤን ውሳኔ በመጋፋት ከተቋማዊ ለውጥ ተቃዋሚዎች ጋራ መቆማቸውን በይፋ አረጋግጠዋል – ‹‹በጣም ደስታ ተሰምቶኛል፤ እኔ በፊት ብቻዬን የኾንኩ ይመስለኝ ነበር፤ ግን ወደ ኋላ ከተመለሳችኁ እናንተ ናችኹ የምትመቱት፤ ቀደም ሲል ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን በነበሩ ሰዓት መልካም አባት ነበሩና ሲዋጉ ሲያደባድቡ የነበሩ ሰዎች እነርሱ ናቸው፤ ቅዱስ አባታችን በነርሱ ነው ተቃጥለው የሞቱት፤ እናንተ ያልተናገራችኹት ነገር የለም፤ ሙሉ ቀን ብትናገሩ ደስ ይላል፤ ንግግራችኹ ሁሉ ጥሩ ነው፤ ግን ሰዎቹ ምንድን ነው በአቋራጭ ቤተ ክርስቲያኒቱን ተረክበው እንደፈለገ ሊያደርጉ ነበር፤ እናንተ ባትነቁ ኖሮ ባቋራጭ ሊረከቧት ነበር፤ ቤተ መንግሥቱንም ቤተ ክህነቱንም ተረክበው እኛን እንደ ውሻ እንጀራ ሊጥሉልን ነው፤ እንደዚህ ነው ዓላማቸው ብዙዎቻችን አልገባንም እንጂ፤ ስለዚህ ቅዱስ አባታችን መልስ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ ይህ ካልኾነ ወደ ሌላ አቅጣጫ እንደሚሄድ ነው እያሳዩ ያሉት፤ ቅዱስ አባታችን፡፡ እና እንዳትመለሱ ነው አደራ የምላችኹ፡፡›› /አቡነ ሳዊሮስ የእነኃይሌን እብሪት በማሞጎስ በፓትርያርኩና በስምንት ሊቃነ ጳጳሳት ፊት ከተናገሩት/ 

ፓትርያርኩ ለአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ ክንውን ከሰጡት አባታዊ መመሪያ በተፃራሪ በእነ ኃይሌ ኣብርሃ ለሚመራው የተቃዋሚ ነኝ ባይ ወሮበላ ስብስብ ፊት በመስጠት የሚያሳዩት የመደራደር ዝንባሌ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱና በተቋማዊ ለውጥ ኃይሎች ትዝብት ውስጥ ጥሏቸዋል፤ ‹‹ተጠርቼ መጥቼ የእርስዎ ረዳት የኾንኩትና ደፋ ቀና የምለው የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤን ውሳኔና የቅዱስነትዎን መመሪያ ለማስከበር ነው፤ አቋምዎን በግልጽ ያሳውቁኝ!›› /ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ/

Friday 3 January 2014

እነሆ የጌታ ልደት ደረሰ

ከታምራት ፍሰሃ
ፌስቡክ ገጽ ላይ የተወሰደ

እነሆ የጌታ ልደት ደረሰ ፡ የጭፈራ ጊዜም ደረሰ ፡ የዳንስና የእስክስታ የመጠጥና የዝሙት ጊዜም ደረሰ። ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን የጌታዋን ልደት ድምጿን ከፍ አድርጋ ታውጃለች ፤ የዚህ አለም ገዢ ዲያቢሎስ ደግሞ ይህን ቅዱስ ጥሪ ማንም እንዳይሰማው ይህን አለም በልዩ ጩኸት በክሎታል ፤ ጭኸቱንም በሚዲያዎች በኩል ያደርጋል። “እንኳን ለጌታ ልደት አደረሳችሁ” ይሉናል። ቀጠል አድርገውም “እዚህ ክለብ ብትሄዱ ለገና ልዩ ዝግጅት ተዘጋጅቷል ፡ ጭፈራው ዘፈኑ ሌላ ነው ፡ መጠጡ ምግቡ ልዩ ነው ፡ ሆይታው ሞቅታው ልዩ ነው ፡ ኑ ና ጌታችሁን እያሳዘናችሁ የዲያቢሎስን ፈቃድ ፈፅሙ” ሲሉ በጥበብ እንሰማቸዋለን፤ በጌታችን ልደት ሰይጣን የሚከብርበት ፡ በክርስቲያኖች ልደት ዲያቢሎስ የሚደምቅበት ፡ በመድሃኒት ክርስቶስ መገለጥ ፡ የዚህ አለም ገዢ ሃሳዊው መሲህ የሚታይበት ይህ ዘመን እንደምን ክፉ ነው?

ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ በማህበረ ቅዱሳን


ሰበር-ዜና ውስጠ ተሃድሶ የሆኑ ጥቂት ሰባክያን አንገታቸውን ቀና ቀና ማድረግ ጀመሩ

 ሱላማጢስ
በቅርቡ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተጀመረውን ሥር ነቀል አስተዳደራዊ ለውጥ ተከትሎ ብቅ ብቅ ያሉ ውስጣቸው ተሃድሶ የሆኑ ጥቂት ሰባክያንና የአድባራት አስተዳዳሪዎች በቤተ ክርስቲያኒቱ የተስፋፋውን የኑፋቄና የሙስናን በሽታ ከሥሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነቅሎ ለመጣል በሚደረገው ከፍተኛ እንቅስቃሴ የተነሳ ይኸው በሽታ የተቆራኛቸው እነ መላከ መንክራት ኃይሌ አብርሃ፣ አባ ሠረቀ እና ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ፣ ሊቀ ትጉሃን ዘካርስ፣ መላከ ብስራት መላክ አበባውን ጨምሮ በሙስናና በኑፋቄ የተጨማለቁ ግለሰቦች ለለውጡ እንቅፋት ለመሆን ዋና ተዋናዮች ናቸው፡፡