Wednesday 20 February 2013

ሰበር ዜና - አቡነ ሳሙኤል በካህናትና ምእመናንን ጥቆማ (popular vote?) በከፍተኛ ብልጫ መሩ


የስድስተኛው ፓትርያሪክ አስመራጭ ኮሚቴ፣ ካህናትና ምእመናን ቀጣዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባት ሊኾን ይገባል ያሉትን እንዲጠቁሙ ባስተላለፈው ጥሪ መሠረት ከተበሰበሰቡት በሺሕዎች ከሚቆጠሩ ካህናትና ምእመናን ጥቆማዎች መካከል፣ የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል እጅግ ከፍተኛውን የጠቋሚዎች ቁጥር በማግኘት በከፍተኛ ብልጫ መምራታቸውን ለምርጫው ሂደት ቅርበት ያላቸው ምንጮቸ ገለጹ፡፡

ከየካቲት 1 - 8 ቀን 2005 ዓ.ም በተሰበሰበውና ከቅዳሜ የካቲት 9 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው አግባብነት ያላቸው ጥቆማዎች ቆጠራ ከአንደኛው እስከ ሦስተኛ የወጡ አባቶች ማንነት ተለይቷል፡፡ በዚህም መሠረት ካህኑንና ምእመኑን በስፋት ለማሳተፍ በተሰበሰበው ጥቆማ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል በእጅግ ከፍተኛ የጠቋሚዎች ቁጥር የመጀመሪያውን ደረጃ በመያዝ መምራታቸው ተረጋግጧል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል፣በሦስተኛ ደረጃ ደግሞ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የከፍተኛ ጠቋሚዎችን ቁጥር ማግኘታቸው ተገልጧል፡፡

ኮሚቴው በጠቋሚዎቻቸው ብዛት አራተኛና አምስተኛ ደረጃ ያገኙትን የተቀሩትን ሁለት አባቶች ማንነት በነገው ዕለት በሚያካሂደው ቆጠራ እንደሚያውቃቸው ይጠበቃል፡፡ የጥቆማውን ውጤቶችና ምልከታዎች እንደ ግብአት (popular vote?) በመያዝ በምርጫ ሕጉ በሰፈረው ድንጋጌ በተጨማሪ መመዘኛዎች ለቅዱስ ሲኖዶስ የሚያቀርባቸውን አምስት አባቶች የካቲት 14 ቀን እንደሚያቀርብ መገለጹ ይታወሳል፡፡ አሁን ሾልኮ የተሰማው የጥቆማ ደረጃ ውጤት፣ የተጠቀሱትን ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ከአምስቱ ዕጩዎች ለመካተት ያበቃቸው እንደኾነ ቆይተን የምናየው ይኾናል፡፡

የዜናው ዝርዝር ይቀጥላል፡፡

የውጪውን ጠላት ለመመከት በቅድሚያ የውስጥ ችግሮቻችንን ማስወገድ ይኖርብናል


ቤተ ክርስቲያን አልተከፈለችም” በሚለው መጣጥፍ መነሻነት የተዘጋጀ ….


(ከመልዐከ ብሥራት፣ ቨርጂኒያ/PDF)፦ ጌታቸው ኃይሌ ናቸው ለዚህ ጽሑፌ መነሻ የሆኑኝ።በቅድሚያ ልባዊ ምሥጋናዬና አክብሮቴ ይድረሳቸው፡፡ በዚህ ጽሑፌ የምናገረው በእውነት ለቤተክርስቲያን ለሚጨነቁ ምዕመናንና አገልጋዮች ብቻ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ላለፉት ሃያ አንድዓመታት በታላቅ ፈተና ውስጥ አልፋለች፡፡ አሁንም እያለፈች ነው፡፡ እግዚአብሔር አይበለውናምናልባት የከፋው ፈተና ያለው ከፊት ለፊታችን ሳይሆን አይቀርም፡፡ የዚህም ሰበቡ ችግሮቻችንንበቅጡ ካለመረዳታችንና ከቸልተኝነታችን የመጣ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ለመሆኑ የቤተ ክርስቲያናችንችግሮች በተለይ በውጪው ዓለም ምንና ምን ናቸው?

የውጪውን ጠላት ለመመከት በቅድሚያ የውስጥ ችግሮቻችንን ማስወገድ ይኖርብናል


ቤተ ክርስቲያን አልተከፈለችም” በሚለው መጣጥፍ መነሻነት የተዘጋጀ ….


(ከመልዐከ ብሥራት፣ ቨርጂኒያ/PDF)፦ ጌታቸው ኃይሌ ናቸው ለዚህ ጽሑፌ መነሻ የሆኑኝ።በቅድሚያ ልባዊ ምሥጋናዬና አክብሮቴ ይድረሳቸው፡፡ በዚህ ጽሑፌ የምናገረው በእውነት ለቤተክርስቲያን ለሚጨነቁ ምዕመናንና አገልጋዮች ብቻ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ላለፉት ሃያ አንድዓመታት በታላቅ ፈተና ውስጥ አልፋለች፡፡ አሁንም እያለፈች ነው፡፡ እግዚአብሔር አይበለውናምናልባት የከፋው ፈተና ያለው ከፊት ለፊታችን ሳይሆን አይቀርም፡፡ የዚህም ሰበቡ ችግሮቻችንንበቅጡ ካለመረዳታችንና ከቸልተኝነታችን የመጣ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ለመሆኑ የቤተ ክርስቲያናችንችግሮች በተለይ በውጪው ዓለም ምንና ምን ናቸው?

አስታራቂ ጉባኤው መግለጫ አወጣ


(ደጀ ሰላም፤ የካቲት 13/2005 ዓ.ም፤ ፌብሩዋሪ 20/2013/ PDF)፦ በአባቶች መካከል የተፈጠረውን መለያየት ላማራቅና ዕርቅ ለማውረድ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ የቆየው የሰላምና አንድነት ጉባኤ ጉዳዩን አስመልክቶ መግለጫ አወጣ። የመግለጫው ምክንያት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ጉባኤ ላለፉት ሦስት ዓመታት በአገር ቤትና በውጭው ዓለም የሚገኙ አባቶችን በማስማማት ቤተ ክርስቲያንን አንድ ለማድረግ ያደረገውን ከፍተኛ ጥረት በዝርዝር ለመግለጽና የዕርቁ ሒደት ምን ይመስል እንደነበር በኢትዮጵያም ሆነ በመላው ዓለም ለሚኖሩ መላው ኦርቶዶክሳውያን ካህናት፣ ምእመናንና የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምርን እንዲያውቁት ለመግለጽ ነው” ያለው መግለጫ ዝርዝር ሐሳቦችን አካቷል። ሙሉ ቃሉን ከዚህ በታች ተመልከቱ።