Friday 7 February 2014

"እግዚኦ አርእየኒ እመከ = አቤቱ እናትህን አሳየኝ"

በቴዎድሮስ በለጠ

"ሰባኪው" በአትሮንሱ ላይ "ቆሟል" .......የቆመበትን እንኳ አያውቅ ( ሊቁ ድንግልን አትሮንሱ ለቃለ አብ ይላታልና...)

ምዕመናን ይጠይቃሉ " ስለ ድንግል ማርያም አስተምረን" ?
ጥያቄውን "ይመልስባቸዋል" እንዲህ ሲል "እኛ እዚህ ድረስ የመጣነው ጌታን ልንሰብክላችሁ እንጂ ስለ ማርያም ልናወራላችሁ አይደለም.... እስኪ ቅዱስ ጳውሎስን ተመልከቱ ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ ስለ ሶምሶንም ስለ ዮፍታሔም""""እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛል አለ እሱ ጊዜ ያለው ስለ ጌታ ብቻ ለመመስከር ነው...."
ይህ በአይሁድ ምኩራብ ፥ በተንባላት አውድ አልያም በመናፍቃን አዳራሽ የተነገረ እንዳይመስላችሁ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን መድረክ ላይ በድፍረት የተፈጸመ እንጂ :: እውነትም ሥፍራው የምሕረት አደባባይ ነው አምላክ ለቁጣና ለመአት የቅጣት ሠይፉን የሚያዘገይበት ለትዕግስትና ለይቅርታ የፍቅር እጁን የሚዘረጋበት "አውደ ምሕረት"! .... እንግዲህ ምን እንላለን "እግዚኦ ተዘከራ ለአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ሀለወት እምጽንፍ እስከ አጽናፈ ዓለም"