Thursday 26 July 2012



መላእክትን ‹‹ያድናሉ›› ማለት ስሕተት ነውን?



ለመሆኑ መላእክት ማዳን ይችላሉ ማለት ስሕተት ነውን? ዛሬ ዛሬብዙዎች መናፍቃን መላእክትን ‹‹ያድናሉ›› ማለት እንደ ስሕተትና 
እንደ ክህደት ቆጥረውት ሲናገሩ መስማት የተለመደ ሆኗል፡፡ ለምንሲባሉም መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹መዳን በሌላ በማንም የለም›› 
በማለት ያለአገባቡ ጥቅስ ይጠቅሳሉ፡፡

በእርግጥ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹መዳን በሌላ በማንም የለም›› ይላል፡፡ይሁን እንጂ ይህ መላእክት አያድኑም ማለት አይደለም፡፡  
ቅዱስ ዳዊት በግልጥ ‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያይሰፍራል፤ ያድናቸውማል›› ይላል፡፡ (መዝ33.7) ጥቅሱ
‹‹ያድናቸውማል›› ማለቱን ልብ በሉ፡፡ መላእክት የማያድኑ ቢሆኑ ኖሮቅዱስ ዳዊት በዚህ መልኩ ግልጥ አድርጎ ‹‹ያድናቸውማል››
ይል ነበር?መጽሐፍ ቅዱስ ከመሰከረው እውነት የሚበልጥ ዕውቀት አለንን? እርሱ‹‹ያድናሉ›› እያለ እኛ ‹‹አያድኑም›› ብንል ምን
ማለታችን ነውይህጥቅስ ውሸት ነውንይህንን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል እንታዘዘዋለን?እናምነዋለንወይስ ልናርመው እንወዳለን?