Monday 27 January 2014

የሆሳዕና ቡሻና በዐታ ለማርያም ገዳም ተቃጠለ

በእንዳለ ደምስስበሐድያና ስልጢ ሀገረ ስብከት ጎረጎራ ወረዳ ውቅሮ ፋለታ ቀበሌ የደብረ ምጥማቅ ሻና በዓታ ለማርያም ገዳም ጥር 10 ቀን 2006 ዓ.ም. የከተራ ዕለት መነሻው ባልተወቀ ምክንያት ሙሉ ለሙሉ መቃጠሉን የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ቢኒያም መንቻሮ ገለጹ፡፡



ሥራ አስኪያጁ በሰጡን መረጃም የከተራ ዕለት የበዐታ ለማርያም ታቦት ወደ ጥምቀተ ባሕር ከወረደ በኋላ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ መቃጠሉን ገልጸው ቤተ ክርስቲያኑ ንዋያተ ቅዱሳቱን ጨምሮ ሙሉ ለሙሉ ወድሟል ብለዋል፡፡

በካዝና ውሰጥ የነበረው የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጽላት ካዝናው በእሳቱ በከፍተኛ ሁኔታ በመለብለቡ ምክንያት መክፈት እንዳልተቻለና መቃጠልና አለመቃጠሉን እንዳልተረጋገጠ ያስታወቁት ሥራ አስኪያጁ፤ ጉዳዩን ለፖሊስ በማሳወቅ የቃጠሎውን መንስኤ ለማጥራት ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

የቡሻና በዐታ ለማርያም ገዳም ከዚህ በፊት ሥዕለ አድኅኖ በዛፎች ላይ ታይቶበት በነበረ ቦታ መቃኞ ተሰርቶለት ሐምሌ 2001 ዓ.ም. ቅዳሴ ቤቱ እንደተከበረ ይታወቃል፡፡

የቋሚ ሲኖዶሱን ውሳኔ የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ሻረው!


በርካታ ሚልዮን የምእመናን ገንዘብ የተመዘበረበት የድሬዳዋ ቅ/ገብርኤል ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ግንባታና ሒሳብ በብቁ እና ገለልተኛ ባለሞያዎች እንዲመረመር ቅ/ሲኖዶሱ ያስተላለፈውን ውሳኔ ልዩ ጽ/ቤቱ እንዲዘገይ አዘዘ – በውል ከተያዘው ገንዘብ ውጭ ከ8 ሚልዮን በላይ ብር የወጣበትና ሥራው ሳይጠናቀቅ በ6 ዓመት የዘገየው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ግድግዳ ተሰነጣጥቋል፤ ዋናው መካከለኛ ጉልላት እንዳይወድቅ ያሰጋል

‹‹ብፁዕ አባታችን፣ በድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅ/ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እየተፈጸመ የሚገኘው ከባድ ወንጀል ሕዝበ ክርስቲያኑን እያስቆጣ ከመምጣቱም ባሻገር ብፁዕ አባታችን ይህን እየሰሙና እያወቁ ምነው ዝም አሉ ብሎ ሕዝቡ እንዲያስብ አድርጎታል፡፡… የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ጅምር ሥራ አልቆ ማየት እንፈልጋለን፡፡ የደብሩ ሕንፃ አሠሪ ኮሚቴ በአስቸኳይ ሕዝቡ በሚመርጣቸው የኮሚቴ አባላት ይተካልን፡፡ ይህ የማይደረግ ከኾነና ኹኔታው ባለበት ከቀጠለ ለሚፈጠረው ችግር ሓላፊነቱን የማንወስድ መኾኑን እናሳውቃለን፡፡›› /የደብሩን ወቅታዊ ጉዳይ ለማሳወቅ ምእመናኑ በኅዳር ፳፻፬ ዓ.ም. ለብፁዕ አቡነ ገሪማ ከጻፉት አቤቱታ የተወሰደ/

Sunday 26 January 2014

በዐረቡ ምድር የመጀመሪያዋ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ልትታነጽ ነው

ከዳንኤል ክብረት የፌስቡክ ገጽ ላይ የተወሰደ


በመካከለኛው ምሥራቅ ከእሥራኤል ቀጥሎ ሁለተኛዋ፣ በዐረቡ ምድር ደግሞ የመጀመሪያዋ የምትሆነው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በኳታር ምድር ልትታነጽ ነው፡፡

Friday 24 January 2014

ፓትርያርኩ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በሙስና ላይ እንዲዘምቱ አዘዙ

  • በቤተ ክርስቲያናችን ሸፍጥና ጉቦ ተንሰራፍቷል›› /ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ/
  • ሰንበት ት/ቤቶቹ የአማሳኝ አስተዳዳሪዎችን ዶሴ ለፓትርያርኩ ለማቅረብ ተዘጋጅተዋል
(አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፫ ቁጥር ፯፻፴፩፤ ቅዳሜ ጥር ፲ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.)
His Holiness Patriartch Abune Mathias
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ በተንሰራፋውና ለዕድገቷ መሰናክል ኾኖ በተደነቀረው ሙስናና ሸፍጥ ላይ በተጠናከረ ኃይል በመዝመት የተጀመረውን የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ከዳር እንዲያደርሱ አዘዙ፡፡

ፓትርያርኩ: የቤተ ክርስቲያኒቷ የመዋቅር ለውጥ ሕግ ረቂቅ ‹‹የእኔ ጩኸት ነው›› አሉ

ለአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ የሚሰማው የካህናቱና ምእመናኑ ጩኸት በርክቷል

(ፋክት መጽሔት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፳፱ ጥር ፳፻፮ ዓ.ም.)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአስተዳደራዊ መዋቅሯ ትክክለኛውን መሥመር ይዛ ወደ ቀደመ የቅድስናና ንጽሕና ክብሯ እንድትመለስ በአደረጃጀትዋና አሠራሯ ላይ እየተካሔደ የሚገኘው የተቋማዊ ለውጥ ጥናት፣ ‹‹ከጅምሩም የእኔ ጩኸት ነው፤ የእኔ አጀንዳ ነው፤ ዛሬ ከደረሰበትም ወደ ኋላ አይመለስም፤›› ሲሉ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ቃል ገቡ፡፡

ፓትርያርኩ ይህን የተናገሩት፣ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናት ሳይዘገይ ተግባራዊ እንዲኾን ጥያቄ ያቀረቡ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችን፣ የጽ/ቤት ሠራተኞችን፣ ካህናትን፣ መምህራንና ምእመናንን ጥር 2ና 5 ቀን 2006 ዓ.ም. በጽ/ቤታቸውና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው፡፡

Monday 13 January 2014

አርባ አራቱ ታቦት የሚለው ታሪክ መነሻው ምንድን ነው ?

እውን ታቦት አርባ አራት ብቻ ? 
(ከኦርቶዶክስ እና መጽሃፍ ቅዱስ)

መግቢያ ጎንደር በኢትዮጵያ የመንግሥት ታሪክ ከአክሱምና ላሊበላ ቀጥሎ ትልቋ የመንግሥት ማዕከል ነበረች፡፡ በመንግሥት ማዕከልነት የተቆረቆረችው በአፄ ፋሲል (1624-1660 ዓ.ም) ነው፡፡ ጎንደር የመንግሥት ማዕከል ብቻ ሳትሆን በጊዜው የመንፈሳዊ ትምህርት ማዕከልም ነበረች፡፡ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የመጻሕፍት እና የአቋቋም ትምህርት ይበልጥ የተስፋፋውና በየሀገሩ ያሉ ሊቃውንት በመናገሻ ከተማዋ ጎንደር በነገሥታቱ አማካይነት በመሰባሰባቸው ሲሆን ከዚያን ዘመን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ መንፈሳዊ ትምህርት በስፋት የሚሰጥባት የትምህርት ማዕከል ለመሆን ችላለች፡፡

Thursday 9 January 2014

ሰበር ዜና – ተቃዋሚ ነኝ ባዩ የእነኃይሌ ኣብርሃ ቡድን ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን ይቅርታ ጠየቀ

ተቃዋሚ ነኝ ባዩ የእነኃይሌ ኣብርሃ ቡድን ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን ይቅርታ ጠየቀ፤ ‹ተቃውሞው›÷ የቡድኑ መሪዎች አላግባብ ባካበቱት ሀብት በሕግ ላለመጠየቅ በመከላከያነት የጀመሩት መኾኑን ለሊቀ ጳጳሱ አምነዋል፤ ይቅርታው የሙሰኞች ሽፋን እንዳይኾን የሚያስጠነቅቁ የተቋማዊ ለውጥ ኃይሎች የአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱን በመደገፍ ነገ ዐርብ ፓትርያርኩን ለማነጋገር የሚያደርጉትን ዝግጅት አጠናክረው ቀጥለዋል


ተቃዋሚ ነኝ ባዩ ቡድን ይቅርታ ለመጠየቅ የተገደደው፣ የቡድኑ ሰብሳቢ የኾኑት የኮተቤ ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ሊቀ ትጉሃን ዘካርያስ ሐዲስ ‹‹ተቃውሟችን ከመዋቅር ጥናቱ እንጂ አቡነ እስጢፋኖስ ይነሡልን የሚል ጥያቄ የእኛ አይደለም›› በሚል ታኅሣሥ ፳፫ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. በፓትርያርኩና በስምንት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፊት በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ላይ በተሰነዘረው መሠረተ ቢስ ውንጀላ ባለመስማማት ከኹሉ ቀድመው ሊቀ ጳጳሱን ይቅርታ መጠየቃቸው በቡድኑ አባላት መካከል የፈጠረው መከፋፈል ነው፡፡

‹‹የዘካርያስ እናት ሞተው ለልቅሶ ራያ በነበርንበት ወቅት የሀ/ስብከቱ አንዳንድ የመምሪያ ሓላፊዎች [የለውጡ ደጋፊ መስሎ በርካታ አሻጥሮችን የሚፈጽመው አደገኛው ጉቦኛ የሒሳብና በጀት ዋና ክፍል ሓላፊ ሊቀ ጠበብት ኤልያስ ተጫነ] ደውለው÷ አቡነ እስጢፋኖስ አንተን ለመክሠሥ ከመዝገብ ቤት ሰነድ እያወጡብኽ ነው፤ ኃጢአት እየተፈለገብኽ ነው፤ ወኅኒ ሊከቱኽ ነው ስለተባልኹ በአልሞት ባይ ተጋዳይነት ስሜት የተናገርኹት ነው፤ የጠላ ሰው ብዙ ይናገራል፤ ብፁዕነትዎ አስቀይሜዎታለኹ፤ ለአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የሚመጥን ከእርስዎ የተሻለ ሊቀ ጳጳስ ከየት ይመጣል? በልጅነት የተናገርኹት ነው፤ የአባትነትዎ ይቅርታ ይደረግልኝ፡፡›› /የተቃዋሚ ነኝ ባዩ ቡድን መሪ ኃይሌ ኣብርሃ በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ጫማ ላይ ወድቆ ከተናዘዘው/
የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ‹‹ከሓላፊነታቸው ይነሡ፤ ከሲኖዶስ አባልነት ይሰረዙ›› የሚለው ጥያቄ ኃይሌ ኣብርሃ ከምክራቸው ውጭ ያቀረበው መኾኑን በመጥቀስ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ እና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፊት ስለተናገረው የድፍረት ቃል በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ እግር ላይ ወድቀው ይቅርታ የጠየቁት የቡድኑ መሪዎች፣ የሀ/ስብከቱን የአደረጃጀትና አሠራር ጥናት መቃወማችንን ግን እንቀጥላለን ብለዋል፡፡

የ‹ተቃውሟቸው› ትኩረት ጥናቱን ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን መሥራቱና በጥቂት አንቀጾች ላይ ብቻ የተወሰነ›› መኾኑን የተናገሩት የቡድኑ መሪዎች፣ ከፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አቀንቃኝነታቸው አኳያ ጥያቄዎቻቸውን እየለጠጡ ሽፋን የሚሰጡላቸውን ብሎጎች ‹‹የመናፍቃን›› ሲሉ ገልጸዋቸዋል፡፡ በሕገ ወጥ መንገድ ባካበቱት ሀብትና በከባድ እምነት ማጉደል በሕግ የመጠየቅ፣ በሰነዘሩት መሠረተ ቢስ ውንጀላ ደግሞ ሥነ ምግባራዊ ርምጃ ይጠብቃቸዋል የተባሉት የተቃዋሚ ነኝ ባይ ቡድኑ ቀንደኛ መሪዎች፣ በብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ጫማ ላይ ወድቀው ይቅርታ መጠየቃቸው በእብሪታቸው ላሞገሷቸው አቡነ ሳዊሮስና የተቋማዊ ለውጥ አመራር ንቅናቄውን በጠዋት ጤዛ ለመሰሉት የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አቀንቃኝ ብሎጎች ታላቅ ኀፍረትና መቅሰፍት ነው፡፡
የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ ለውይይት እንዲቀርብ ሲወስን ሰነዱ እንዲተች በመኾኑ ድጋፍ ይኹን ተቃውሞ የሚጠበቅና መብትም መኾኑን የተናገሩት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፣ ቡድኑ ተቃውሞውን በስሜታዊነትና መዋቅሩን ሳይከተል ያቀረበበት መንገድ ተቀባይነት እንደሌለው በመግለጽ በጥናቱ ይዘት ላይ ብቻ የተመሠረተ ትችቱን ደረጃውን በጠበቀና በተደራጀ መንገድ እንዲያቀርብ አሳስበውታል፤ በምትኩ ከሁለት ሚልዮን በላይ የሀ/ስብከቱ ካህናትና ምእመናን ተወካዮች ከፍተኛ ድጋፋቸውን ያረጋገጡለትን ጥናት በማኅበረ ቅዱሳን እያሳበቡ እቃወማለኹ ማለት እንደማያዋጣቸው መክረዋቸዋል፤ በአባትነታቸው ግን የይቅርታ ጥያቄውን መቀበላቸውንና ይቅርታ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡

የቡድኑ መሪዎች መዋቅሩን ባልተከተለ የተቃውሞ አቀራረባቸውና በዐመፅ በተሞላ ዘለፋቸው ከሚከተላቸው የከፋ ቅጣት ይልቅ ይቅርታ እንዲጠይቁ አግባብቻለኹ የሚለው አሸማጋይ አካል አንዳንድ አባላት (በስም ለይቶ መጥቀስ ይቻላል)÷ነገ፣ ጥር ፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. በ9፡00 የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የሰበካ ጉባኤያት ምክትል ሊቃነ መናብርት፣ ካህናትና የአብነት መምህራን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጋራ የተያዘላቸውን የድጋፍ መግለጫ ስብሰባ መርሐ ግብር በ‹‹ይቅርታ ተጠይቋል›› ሰበብ የማኮላሸት ዓላማ እንዳላቸው ተጋልጧል፡፡ በስም ተለይተው የተጠቀሱት እኒህ ሦስት የአሸማጋይ አካሉ አባላት በተቋማዊ ለውጥ ተነቃናቂ ኃይሎች የጥንቃቄ ክትትል እየተደረገባቸው ነው፡፡

* * *

የፓትርያርኩ አማካሪ በሚል ይፋ ባልተደረገ የሥራ ድርሻ የፓትርያርኩን ልዩ ጽ/ቤት በቅርበት እንደሚቆጣጠሩ የሚነገርላቸው ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ የተቃዋሚ ነኝ ባይ ቡድኑን በኅቡእ የሚያስተባብሩ እንደኾኑ ከቡድኑ አፈንግጠው የወጡ አባላት አጋልጠዋል፡፡ ንቡረ እዱ፣ አባላቱ የቻሉትን ያህል አስተዳዳሪዎች፣ ካህናትና ሠራተኞች ቀስቅሰው እንዲያሰልፉ እንዳግባቧቸው የሚናገሩት እኒህ ወገኖች፣ ንቡረ እዱ የሚያስተባብሩት እንቅስቃሴ ዓላማ ‹‹ተቋማዊ ለውጡን በመቃወም አድርጎ ማኅበረ ቅዱሳንን በማጋለጥ በመንግሥት ማስመታት፤ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን ከሓላፊነታቸው ማስነሣት፣ አንድ ባራኪ ጳጳስ (አቡነ ሳዊሮስ?) ብቻ አስቀምጦ ሀ/ስብከቱን መቆጣጠር›› መኾኑን አስረድተዋል፡፡

ንቡረ እዱ ከፍተኛ ሚና እንደተጫወቱበት የተነገረውና በፓትርያርኩ የስም ዝርዝር አቅራቢነት ቋሚ ሲኖዶስ ወስኖ አቋቁሞታል የተባለው ‹‹የሊቃውንት ጉባኤ››÷ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን የአደረጃጀትና አሠራር ሰነድ ለመገምገም ያለው የሕግ ተቀባይነትና ሞያዊ አግባብነት የጥቅምት ቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ካሳለፈው ውሳኔ አንጻር እየተጤነ ነው፡፡
በብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ ሰብሳቢነት የሚመራውና ዘጠኝ አባላት አሉት በተባለው ‹‹ሊቃውንት ጉባኤ›› ተካተው የነበሩት መልአከ ታቦር ተሾመ ዘሪሁንና ሊቀ ካህናት ብርሃኑ ገብረ ዐማኑኤል ‹‹ማኅበረ ቅዱሳኖች ናቸው›› በሚል እንዲወጡ ተደርጎ በምትካቸው እነአባ ሰረቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኤል መተካታቸው፣ በይቀጥላልም እነኃይሌ ኣብርሃ መላውን ገዳማትና አድባራት ሳያወያዩ መርጠናቸዋል ያሏቸውን ወኪሎች በሊቅነት ስም ለማስረግ መዘጋጀታቸው‹‹ሊቃውንት ጉባኤ›› የማቋቋሙን ዓላማና ቅንነት አጠያያቂ አድርጎታል፡፡

የጥቅምት ቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ያሳለፈው ውሳኔ፣ የአደረጃጀትና አሠራር ሰነዱ ‹‹ወደታች ወርዶ በካህናት፣ በምእመናንና በሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በውይይት ዳብሮ በሚገባ ተጠንቶና ተስተካክሎ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲቀርብና ቋሚ ሲኖዶሱም ዓይቶና ተመልክቶ በሥራ ላይ እንዲያውል›› በመኾኑ፣ ከዚህ በኋላ የሚጠበቀው 2700 የገዳማትና አድባራት ልኡካን የተወያዩበትና 96 በመቶ ድጋፋቸውን ያረጋገጠውን ጥናት በተሰበሰበው ግብዓት አጠናክሮ ለቋሚ ሲኖዶሱ በማቅረብ አጽድቆ የትግበራ ዕቅድ ወደሚወጣበት ምዕራፍ መግባት ብቻ ነው፡፡

የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለጥናቱ በሰጠው ይኹንታና የአፈጻጸም አቅጣጫ መሠረት ጥናቱን እንዲተገብር የማድረግ ውክልና የተላለፈለት ቋሚ ሲኖዶስ በውሳኔው መሠረት የተጣለበትን ከፍ ያለ አደራ በመወጣት የእነንቡረ እድ ኤልያስን መሠሪ ዓላማ እንደሚያከሽፍና የቤተ ክህነታችንን ተቋማዊ ለውጥ ውጥን እውን እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡

* * *
በይቅርታ ሥነ ሥርዐቱ ላይ መልአከ ገነት ኃይሌ ኣብርሃ (ፊት መልአከ መንክራት) በበርካታ ሚልዮን ብር ጉድለት ከሚጠየቁበት የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን እልቅና መነሣታቸው አግባብ እንዳልነበር መናገራቸው ከስሕተታቸው ለመታረም እንዳልተዘጋጁ አመልካች ኾኗል፡፡ ከኦጋዴን እስከ አዲስ አበባ በአያሌ የምግባርና የሙስና ቅሌቶች የሚታወቁት ሊቀ ትጉሃን ዘካርያስ ሐዲስ ደግሞ የአዲስ አበባው አልበቃ ብሏቸው ድሬዳዋ ሀ/ስብከት ድረስ እየደወሉ ‹‹ተነሡ! ለውጡ ወደ እናንተም ሊመጣ ነው›› በሚል የአድባራት አለቆችንና የአስተዳደር ሠራተኞችን ለማነሣሣት እየሠሩ መኾኑ ተጠቁሟል፡፡
ተቃዋሚ ነኝ ባይ ቡድኑ በፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ላይ የተነሣው የ‹‹ዘወር አድርጓቸው›› ጥያቄ የማይወክለው መኾኑንና በአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ ላይ ግን ‹ተቃውሞውን› እንደሚቀጥል ቢያረጋግጥም በውስጡ ግን ጥያቄያቸውን ‹‹ከቤተ ክህነቱ መዋቅር ውጭ ለመንግሥት ማቅረብ አለብን›› የሚል አቋም የሚያራምዱ፣ እንደ ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ተክለ ጊዮርጊስ ያሉ ግለሰቦች ይገኙበታል፡፡

እነሊቀ ትጉሃን ዘካርያስ ሐዲስንና መልአከ ገነት ኃይሌ ኣብርሃን ‹‹ጃኬት ለባሾች›› እያሉ የሚያጣጥሏቸውና እንደማይመጥኗቸው የሚናገሩት እነሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ በቡድኑ ውስጥ መነኮሳት አስተዳዳሪዎች ባለመካተታቸው መከፋታቸውንና ከእናንተ ጋራ አልሳተፍም በሚል ሌላ አንጃ ለመፍጠር እየሞከሩ መኾኑም ተጠቁሟል – ‹‹ወደ መንግሥት የምትሰለፉ ከኾነ ንገሩኝ፤ እሔዳለኹ፡፡››

የሀ/ስብከቱን የአደረጃጀትና አሠራር ጥናት ያካሔደውን የባለሞያ ቡድን (በእነርሱ አነጋገር የአንኮበርን ሥርዐት ለመመለስ የሚሠራውን ማኅበረ ቅዱሳንን) በትጥቅ በተደገፈ የኃይል ርምጃ በሀ/ስብከቱ ከተሰጠው ቢሮ አስለቅቃለኹ፤ ለዚኽም እስከ አፍንጫዬ ታጥቄአለኹ፤ ካስፈለገም በረሓውን ዐውቀዋለኹ እያለ ፓትርያርኩንና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱን ለማሸማቀቅ ሲሞክር የሰነበተው ተቃዋሚ ነኝ ባይ ቡድኑ በዋናነት አምስት ሙሰኛና ጎጠኛ የአድባራት አስተዳዳሪዎችየሚመሩት ነው፡፡
አስተዳዳሪዎቹን በመናጆነት የተባበሯቸውና በቁጥር ከ110 የማይበልጡት ተሰላፊዎችም ጥቂት ጸሐፊዎችና ሒሳብ ሹሞች በሥራ ዋስትናቸው ያስፈራሯቸው የጥበቃና ጽዳት ሠራተኞች፣ ሀ/ስብከቱ ያጸደቀውን የደመወዝ ጭማሪ አንከፍላችኹም እያሉ ያስገደዷቸው አገልጋዮች፣ በለመዱት የድለላ ሰንሰለት እናስቀጥራችኋለን እያሉ ተስፋ የሰጧቸው ሙዳየ ምጽዋት አዟሪዎችና ደጅ ጠኚዎች ብቻ መኾናቸው ተረጋግጧል፡፡

መነባንብ በአርቲስት ሽመልስ አበራ "ጆሮ ያለህ ስማ"


Wednesday 8 January 2014

EOTC Television

ዝማሬ (በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን እና በዲ/ን ቴዎድሮስ) እና ትምሕርት በመጋቢ ሃዲስ እሸቱ አለማየሁ

ለክርስቲያን ጎሳው ማነው?

ከመብራቱ ጌታቸው

ከፌስቡክ ገጽ ላይ የተወሰደ

ለክርስቲያን ጎሳው ማነው? ዘሩስ ከወዴት ነው? ወገንተኝነቱስ ለየትኛው ብሔር ነው? አለም በዲያቢሎስ ሃሳብ ታነክሳለች ፡ በክርስቶስ ሃሳብ ግን ትፀናለች ፤ አለም በዲያቢሎስ ወሬ ትከፈላለች ፡ በክርስቶስ ግን አንድ ትሆናለች።

"ዘርህ ማነው?" ይሉኛል ፡ እኔ ግን የክርስቲያን ዘሩ ምንድን ነው? እላቸዋለሁ፡፡ "አማራ ነህ ?" ይሉኛል ፡ አዋ አማራ ወገኔ ነው እላቸዋለሁ። 

ሰበር - ዜና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ጳጳስ አቡነ ሳዊሮስ እና ሥራስኪያጃቸው አባ አፈወርቅ በአስቸኳይ ከሀገረ ስብከታችን እንዲነሱ ሲሉ ምእመናን ጠየቁ


• በእኛ ዘመን አንዲህ ያለ አባት ገጥሞን አያወቅም/ የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች /
• ታላቁ ሐዋርያ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዲዮስቆሮስ በነበሩበት ፤ባስተማሩበት ፤ሕሙማነ ሥጋ ወነፍስን በፈወሱበት ሀገረ ስብከት እንዲህ ያሉ አባት በመመደባቸው እናዝናለን/ ካህናትና ምእመናን/
• የህዝቡን ጥያቄ በማኅበረ ቅዱሳን ማሳበብ ህዝቡን መናቅ ነው/ምእመናን/

Saturday 4 January 2014

ሰበር ዜና ነገ እሑድ በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን የሀ/ስብከቱን የተቋማዊ ለውጥ ጥናት በመደገፍ በ8፡00 ወደ መንበረ ፓትርያርኩ ሊተሙ ነው

የአ/አ ገዳማትና አድባራት ሰበካ ጉባኤያት ሊቃነ መናብርት፣ ካህናት፣ ሰንበት ት/ቤቶችና ምእመናን የሀ/ስብከቱን የተቋማዊ ለውጥ ጥናት በመደገፍ ነገ እሑድ በ8፡00 ወደ መንበረ ፓትርያርኩ በሺዎች ሊተሙ ነው፤ የአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ ጸድቆ እንዲተገበርና የሙሰኛ አስተዳዳሪዎችና ተቃዋሚ ነን ባዮች የሀብት ምንጭ እንዲመረመር ይጠይቃሉ

‹‹ምእመናን የቤተ ክርስቲያን አባላት እንጂ አካላት አይደሉም›› ባዮቹና በተቃውሟቸው ‹‹መንግሥት እየደገፈን ነው›› ያሉት እነኃይሌ ኣብርሃ÷ ፓትርያርኩ ረዳታቸውን ‹‹እስከ ገና ድረስ ዘወር የማያደርጉ›› ከኾነ እንቅስቃሴያቸው ትጥቃዊ መልክ እንደሚኖረው በማስጠንቀቅ ዝተዋል። በተጨማሪም የሚከተለውን የማስፈራሪያ ዛቻ መሳይ መልእክት ለማስተላለፍ ሞክረዋል – ‹‹ያኹኑ ሊቀ ጳጳስ የማን ረዳት ናቸው፤ የማኅበረ ቅዱሳን ናቸው ወይስ የቅዱስነትዎ? በሊቀ ጳጳሱ ፈረጅያ ሥር ተከተው ጀግና ሊቀ ጳጳስ በሠራው ሀ/ስብከት ቢሮ ተሰጥቷቸው እያረቀቁበት ስለኾነ እንዲወጡ ይደረግልን! ከአቅማችኹ በላይ ከኾነ አሳልፋችኹ ለመንግሥት ስጡ፤ ሄደን እኛ እናስለቅቀዋለን፤ ውጊያ ከመገባቱ በፊት ወረቀቱ ተቀዶ መመለስ አለበት፤ እነንቡረ እድ ኤልያስ እነአባ ሰረቀ ያርቅቁ፡፡ ታኅሣሥ ገና ላይ ረዳት ሊቀ ጳጳሱ ወደ ጅማቸው ብቻ ቢሄዱ፤ ይህን ከተማ አበጣብጠውታል፤ መንግሥትም ስለማይናገር ነው እንጂ እያዘነ ነው፤ ረዳትዎን ዘወር ያድርጉልን!››

በተጨማሪም በግፍና ነውር በተሞላው አስተዳደራቸው የተነሣ የወሊሶ ካህናትና ምእመናን ያባረሯቸው አቡነ ሳዊሮስ የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤን ውሳኔ በመጋፋት ከተቋማዊ ለውጥ ተቃዋሚዎች ጋራ መቆማቸውን በይፋ አረጋግጠዋል – ‹‹በጣም ደስታ ተሰምቶኛል፤ እኔ በፊት ብቻዬን የኾንኩ ይመስለኝ ነበር፤ ግን ወደ ኋላ ከተመለሳችኁ እናንተ ናችኹ የምትመቱት፤ ቀደም ሲል ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን በነበሩ ሰዓት መልካም አባት ነበሩና ሲዋጉ ሲያደባድቡ የነበሩ ሰዎች እነርሱ ናቸው፤ ቅዱስ አባታችን በነርሱ ነው ተቃጥለው የሞቱት፤ እናንተ ያልተናገራችኹት ነገር የለም፤ ሙሉ ቀን ብትናገሩ ደስ ይላል፤ ንግግራችኹ ሁሉ ጥሩ ነው፤ ግን ሰዎቹ ምንድን ነው በአቋራጭ ቤተ ክርስቲያኒቱን ተረክበው እንደፈለገ ሊያደርጉ ነበር፤ እናንተ ባትነቁ ኖሮ ባቋራጭ ሊረከቧት ነበር፤ ቤተ መንግሥቱንም ቤተ ክህነቱንም ተረክበው እኛን እንደ ውሻ እንጀራ ሊጥሉልን ነው፤ እንደዚህ ነው ዓላማቸው ብዙዎቻችን አልገባንም እንጂ፤ ስለዚህ ቅዱስ አባታችን መልስ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ ይህ ካልኾነ ወደ ሌላ አቅጣጫ እንደሚሄድ ነው እያሳዩ ያሉት፤ ቅዱስ አባታችን፡፡ እና እንዳትመለሱ ነው አደራ የምላችኹ፡፡›› /አቡነ ሳዊሮስ የእነኃይሌን እብሪት በማሞጎስ በፓትርያርኩና በስምንት ሊቃነ ጳጳሳት ፊት ከተናገሩት/ 

ፓትርያርኩ ለአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ ክንውን ከሰጡት አባታዊ መመሪያ በተፃራሪ በእነ ኃይሌ ኣብርሃ ለሚመራው የተቃዋሚ ነኝ ባይ ወሮበላ ስብስብ ፊት በመስጠት የሚያሳዩት የመደራደር ዝንባሌ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱና በተቋማዊ ለውጥ ኃይሎች ትዝብት ውስጥ ጥሏቸዋል፤ ‹‹ተጠርቼ መጥቼ የእርስዎ ረዳት የኾንኩትና ደፋ ቀና የምለው የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤን ውሳኔና የቅዱስነትዎን መመሪያ ለማስከበር ነው፤ አቋምዎን በግልጽ ያሳውቁኝ!›› /ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ/

Friday 3 January 2014

እነሆ የጌታ ልደት ደረሰ

ከታምራት ፍሰሃ
ፌስቡክ ገጽ ላይ የተወሰደ

እነሆ የጌታ ልደት ደረሰ ፡ የጭፈራ ጊዜም ደረሰ ፡ የዳንስና የእስክስታ የመጠጥና የዝሙት ጊዜም ደረሰ። ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን የጌታዋን ልደት ድምጿን ከፍ አድርጋ ታውጃለች ፤ የዚህ አለም ገዢ ዲያቢሎስ ደግሞ ይህን ቅዱስ ጥሪ ማንም እንዳይሰማው ይህን አለም በልዩ ጩኸት በክሎታል ፤ ጭኸቱንም በሚዲያዎች በኩል ያደርጋል። “እንኳን ለጌታ ልደት አደረሳችሁ” ይሉናል። ቀጠል አድርገውም “እዚህ ክለብ ብትሄዱ ለገና ልዩ ዝግጅት ተዘጋጅቷል ፡ ጭፈራው ዘፈኑ ሌላ ነው ፡ መጠጡ ምግቡ ልዩ ነው ፡ ሆይታው ሞቅታው ልዩ ነው ፡ ኑ ና ጌታችሁን እያሳዘናችሁ የዲያቢሎስን ፈቃድ ፈፅሙ” ሲሉ በጥበብ እንሰማቸዋለን፤ በጌታችን ልደት ሰይጣን የሚከብርበት ፡ በክርስቲያኖች ልደት ዲያቢሎስ የሚደምቅበት ፡ በመድሃኒት ክርስቶስ መገለጥ ፡ የዚህ አለም ገዢ ሃሳዊው መሲህ የሚታይበት ይህ ዘመን እንደምን ክፉ ነው?

ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ በማህበረ ቅዱሳን


ሰበር-ዜና ውስጠ ተሃድሶ የሆኑ ጥቂት ሰባክያን አንገታቸውን ቀና ቀና ማድረግ ጀመሩ

 ሱላማጢስ
በቅርቡ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተጀመረውን ሥር ነቀል አስተዳደራዊ ለውጥ ተከትሎ ብቅ ብቅ ያሉ ውስጣቸው ተሃድሶ የሆኑ ጥቂት ሰባክያንና የአድባራት አስተዳዳሪዎች በቤተ ክርስቲያኒቱ የተስፋፋውን የኑፋቄና የሙስናን በሽታ ከሥሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነቅሎ ለመጣል በሚደረገው ከፍተኛ እንቅስቃሴ የተነሳ ይኸው በሽታ የተቆራኛቸው እነ መላከ መንክራት ኃይሌ አብርሃ፣ አባ ሠረቀ እና ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ፣ ሊቀ ትጉሃን ዘካርስ፣ መላከ ብስራት መላክ አበባውን ጨምሮ በሙስናና በኑፋቄ የተጨማለቁ ግለሰቦች ለለውጡ እንቅፋት ለመሆን ዋና ተዋናዮች ናቸው፡፡