Tuesday 26 February 2013

የ5ቱ እጩ ፓትርያርኮች አጭር የሕይወት ታሪክ


PDF http://bit.ly/YwKqd1:- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 6ኛውን ፓትርያርክ ለመምረጥ በዝግጅት ላይ እንደምትገኝ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ አስመራጭ ኮሚቴ በመሠየም እጩ ፓትርያርኮችን ለመምረጥ ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት፤ ከካህናት፤ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች፤ ከማኅበረ ቅዱሳን፤ እንዲሁም ከምእመናን ጥቆማ እንዲያካሔዱ ተደርጓል፡፡ በተካሔደው ጥቆማ መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ጥቆማውን በግብአትነት በመጠቀም አምስት ሊቃነ ጳጳሳትን በእጩነት በማቅረብ የካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አቅርቧል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤም ከየካቲት 16 – 18 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ ውይይት በማካሔድ አምስቱም ሊቃነ ጳጳሳት በእጩነት እንዲቀርቡ አጽድቋል፡፡

Monday 25 February 2013

ታሪክን የኋሊት “ፓትርያርኩን አትምጡ ስንላቸው መጥተው እኛንም በገማ እንቁላል አስደበደቡን” አቡነ ማቲያስ



  • አቡነ ማቲያስ አቀድሳለሁ ነው የምልዎት  እንዲህ አይነቱ ቤተ ክርስቲያን ቢፈርስ ምን ይጎዳል” አቡነ ጳውሎስ
  • እንደ ፖሊሶቹ ቁጥር ማነስና ጥንቃቄ ጉድለት የፓትርያርኩ ተቃዋሚዎች  የፈለጉትን ዓይነት ወንጀል በላያችን ላይ ከመፈጸም የሚያግዳቸው ነገር አልነበረም” አቡነ ማቲያስ በጊዜው የተነሳውን ተቃውሞ  ሲገልፁ
  • “ፓትርያርኩን አጅበን ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስተን ቦልቲሞር ስንደርስ ፤ ተዘጋጅቶ ሲጠብቅ የነበረው ተቃዋሚው የፖለቲካ ቡድን ቀፎው እንደተነካበት ንብ በድንገት ወጥቶ ወረረን ፤ በጣም ቀፋፊ የሆነ ስድብ ውርጅብኝ አወረደብን፡፡
  • አቡነ ጳውሎስ ይጎበኙታል የተባለው ሕንጻ ውስጥ ፈንጂ ተቀብሯል ስለተባለ እርሳቸውና ከእሳቸው ጋር ያሉት 9 ሊቃነ ጳጳሳት እንዲመለሱ ተደርገዋል፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን አባሎች የፓትርያርክ ምርጫ ላይ ድምጽ እንዳይኖራቸው ለማድረግ ዘመቻ ተጀምሯል

  • የማህበረ ቅዱሳን አባል የሆነ ከሀገረ ስብከት ተወክሎ ድምጽ እንዳይሰጥ ትዕዛዝ ተላፏል፡፡
  •  ብጹዕ አቡነ ማቲያስ ያለምንም ተቀናቃኝ የካቲት ሃያ አራት 6ተኛፓትርያርክ ሆነው ይሾማሉ፡

(አንድ አድርገን የካቲት 19 2005 ዓ.ም)፡- የስድስተኛው ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ ባቀረባቸው አምስቱ እጩ ፓትርያርኮች ዙሪያ ቅዱስ ሲኖዶስ ተወያይቶ እጩዎቹን በማጽደቅ ትላንት ጥር 18 2005 ዓ.ም ይፋዊ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል ፤ ይህ ይፋዊ መግለጫ 2791 በላይ ጥቆማዎች እንደደረሱት ገልጿል ፡፡ ለእጩነት የተጠቆሙት አባቶች በጠቅላላ 36 ሲሆኑ 15ቱ በአግባቡ ባለመጠቆማቸው እነርሱን ጥሎ አስራ ዘጠኙ ላይ በተቀመጠው የመመዘኛ መስፈርት መሰረት አምስቱን አሳልፎ ለቅዱስ ሲኖዶስ ማቅረቡን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ኮሚቴው ያከናወነውን ስራ አባ አስጢፋኖስ እንዲህ በማለት ገልጸዋል “የአስመራጭ ኮሚቴው ከአምስት ያልበለጡ ከሶስት ያላነሱ እጩ ፓትርያርኮችን የካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም ለሚካሄደው ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ለማቅረብ ሰፊ ውይይት አድርጓል ፤ በተደረገው ውይይትም አሁን በአገልግሎት ላይ ካሉ ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት መካከል 19 ሊቃነ ጳጳሳትን በቀጣይነት ለማጣራት አሳልፏል ፤ እጩዎቹን ለመለየት የተከተለው መመዘኛም እድሜና ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ነው፡፡”በማለት ገልጸዋል፡፡ አስመራጭ ኮሚቴው ባደረገው ማጣራትም አምስቱን እጩ ፓትርያርኮችን ለይቶ ለቅዱስ ሲኖዶስ አቅርቧል ተብሏል ፡፡ እነርሱም 1ኛ ብጹዕ አቡነ ማቲያስ ፤ 2ተኛ ብጹዕ አቡነ ኤልሳ ፤ 3ተኛ ብጹዕ አቡነ ዮሴፍ ፤ 4ተኛ ብጹዕ አቡነ ሕዝቅኤል እና 5ተኛ ብጹዕ አቡነ ማቴዎስ  መሆናቸው ታውቋል፡፡ የአምስቱ እጩ ፓትርያርኮች ስም የቀረበለት ቅዱስ ሲኖዶስም ማጽደቁን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ “ለመንጋው የሚሆን እረኛ እግዚአብሔር እንዲሰጠን ምዕመናን ፋጣሪያቸው በጸሎት እንዲጠይቁ ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል”ብለዋል፡፡ 

ሽማግሌዎች ብፁዕ አቡነ ሳሙኤልን አነጋገሩ፤ አስመራጩ መግለጫ ሰጠ


(ደጀ ሰላም፤ የካቲት 18/2005 ዓ.ም፤ ፌብሩዋሪ 25/2013/ PDF) ቅዳሜ የካቲት 16/2005 ዓ.ም ቀርበው በአብዛኛው የቅ/ሲኖዶስ አባላት ይሁንታ አግኝተዋል የተባሉት አስምት ሊቃነ ጳጳሳት በመጪው ሐሙስ ለሚካሄደው የፓትርያርክ ምርጫ ያለፉ መሆናቸውን አስመራጭ ኮሚቴው ዛሬ በጋዜጣዊ መግለጫው ገልጿል።


ከፍተኛ ታቃውሞና የከረረ ተግሳጽ የደረሰባቸውን አቡነ ማትያስ ዘኢየሩሳሌምን ጨምሮ ሌሎቹ አራት አባቶች የተካተቱበት የአስመራጭ ኮሚቴው ጥቆማ ለቅ/ሲኖዶስ ቢቀርብም ተጨማሪም ተቀናሽም ሳይደረግበት መጽደቁ ዛሬ ይፋ ሆኗል። በዚህም መሠረት ሐሙስ በሚደረገው ምርጫ ከፍተኛ ቁጥር የሚያገኘው ተወዳዳሪ ስድስተኛ ፓትርያርክ ተብሎ ይሾማል ማለት ነው።

Sunday 24 February 2013

የዕጩዎች ምርጫው እንደፈለጉት ያልሆነላቸው ጳጳሳት ሙግት ገጥመዋል


(ደጀ ሰላም፤ የካቲት 16/2005 ዓ.ም፤ ፌብሩዋሪ 23/2013/PDF)፦ የስድስተኛው  ፓትርያርክ  አስመራጭ   ኮሚቴ  በዛሬው   ዕለት  የዕጩዎቹን  ዝርዝር  ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ባቀረበበት ወቅት ምርጫው በፈቀዱት መልክ አልሔደላቸውም የተባሉ ጳጳሳት ሙግት ገጥመው መዋላቸውን የደጀ ሰላም ምንጮች ገለፁ።


“ፓትርያሪክ እንድሆን የመንግስት ባለሥልጣን አላግባባሁም” (ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል)


‹ካህናትና ምእመናን ለቤተ ክርስቲያንና ለቤተ ክርስቲያን ብለው ብቻ ማሰብ፣ ይገባቸዋል›› - (ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል)


(አዲስአድማስ ጋዜጣ፤ የካቲት 17/2005 ዓ.ም

ፌብሩዋሪ 24/2013/ PDF)፦ የምርጫው ሂደት በይፋ ከተጀመረ አንሥቶና ከዚያም በፊት ቀጣዩ ፓትርያሪክ እንደሚኾኑ ብዙ ከተነገረላቸው ሊቃነ ጳጳሳት መካከል የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል አንዱ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው በፓትርያሪክነት ምርጫው ከሚሳተፉ ከ800 በላይ መራጮች የምርጫ ድጋፍ ለማሰባሰብ በሥልጠና ስም በርካታ ገንዘብ ማውጣታቸውን፤ በሕንፃ ኪራይ፣ በሥራ ምደባ፣ በውጭ ተልእኮና በሹመት አሰጣጥ ለብዙዎች ቃል መግባታቸውን፤ ከዚህም አልፎ ቀጣዩ ፓትርያሪክ እርሳቸው እንደሚኾኑ ራሳቸውን ለመንግሥት አካላት ስለ ማስተዋወቀቸው በአንዳንድ ሚዲያዎች ተዘግቧል፡፡

Wednesday 20 February 2013

ሰበር ዜና - አቡነ ሳሙኤል በካህናትና ምእመናንን ጥቆማ (popular vote?) በከፍተኛ ብልጫ መሩ


የስድስተኛው ፓትርያሪክ አስመራጭ ኮሚቴ፣ ካህናትና ምእመናን ቀጣዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባት ሊኾን ይገባል ያሉትን እንዲጠቁሙ ባስተላለፈው ጥሪ መሠረት ከተበሰበሰቡት በሺሕዎች ከሚቆጠሩ ካህናትና ምእመናን ጥቆማዎች መካከል፣ የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል እጅግ ከፍተኛውን የጠቋሚዎች ቁጥር በማግኘት በከፍተኛ ብልጫ መምራታቸውን ለምርጫው ሂደት ቅርበት ያላቸው ምንጮቸ ገለጹ፡፡

ከየካቲት 1 - 8 ቀን 2005 ዓ.ም በተሰበሰበውና ከቅዳሜ የካቲት 9 ቀን ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው አግባብነት ያላቸው ጥቆማዎች ቆጠራ ከአንደኛው እስከ ሦስተኛ የወጡ አባቶች ማንነት ተለይቷል፡፡ በዚህም መሠረት ካህኑንና ምእመኑን በስፋት ለማሳተፍ በተሰበሰበው ጥቆማ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል በእጅግ ከፍተኛ የጠቋሚዎች ቁጥር የመጀመሪያውን ደረጃ በመያዝ መምራታቸው ተረጋግጧል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል፣በሦስተኛ ደረጃ ደግሞ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የከፍተኛ ጠቋሚዎችን ቁጥር ማግኘታቸው ተገልጧል፡፡

ኮሚቴው በጠቋሚዎቻቸው ብዛት አራተኛና አምስተኛ ደረጃ ያገኙትን የተቀሩትን ሁለት አባቶች ማንነት በነገው ዕለት በሚያካሂደው ቆጠራ እንደሚያውቃቸው ይጠበቃል፡፡ የጥቆማውን ውጤቶችና ምልከታዎች እንደ ግብአት (popular vote?) በመያዝ በምርጫ ሕጉ በሰፈረው ድንጋጌ በተጨማሪ መመዘኛዎች ለቅዱስ ሲኖዶስ የሚያቀርባቸውን አምስት አባቶች የካቲት 14 ቀን እንደሚያቀርብ መገለጹ ይታወሳል፡፡ አሁን ሾልኮ የተሰማው የጥቆማ ደረጃ ውጤት፣ የተጠቀሱትን ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ከአምስቱ ዕጩዎች ለመካተት ያበቃቸው እንደኾነ ቆይተን የምናየው ይኾናል፡፡

የዜናው ዝርዝር ይቀጥላል፡፡

የውጪውን ጠላት ለመመከት በቅድሚያ የውስጥ ችግሮቻችንን ማስወገድ ይኖርብናል


ቤተ ክርስቲያን አልተከፈለችም” በሚለው መጣጥፍ መነሻነት የተዘጋጀ ….


(ከመልዐከ ብሥራት፣ ቨርጂኒያ/PDF)፦ ጌታቸው ኃይሌ ናቸው ለዚህ ጽሑፌ መነሻ የሆኑኝ።በቅድሚያ ልባዊ ምሥጋናዬና አክብሮቴ ይድረሳቸው፡፡ በዚህ ጽሑፌ የምናገረው በእውነት ለቤተክርስቲያን ለሚጨነቁ ምዕመናንና አገልጋዮች ብቻ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ላለፉት ሃያ አንድዓመታት በታላቅ ፈተና ውስጥ አልፋለች፡፡ አሁንም እያለፈች ነው፡፡ እግዚአብሔር አይበለውናምናልባት የከፋው ፈተና ያለው ከፊት ለፊታችን ሳይሆን አይቀርም፡፡ የዚህም ሰበቡ ችግሮቻችንንበቅጡ ካለመረዳታችንና ከቸልተኝነታችን የመጣ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ለመሆኑ የቤተ ክርስቲያናችንችግሮች በተለይ በውጪው ዓለም ምንና ምን ናቸው?

የውጪውን ጠላት ለመመከት በቅድሚያ የውስጥ ችግሮቻችንን ማስወገድ ይኖርብናል


ቤተ ክርስቲያን አልተከፈለችም” በሚለው መጣጥፍ መነሻነት የተዘጋጀ ….


(ከመልዐከ ብሥራት፣ ቨርጂኒያ/PDF)፦ ጌታቸው ኃይሌ ናቸው ለዚህ ጽሑፌ መነሻ የሆኑኝ።በቅድሚያ ልባዊ ምሥጋናዬና አክብሮቴ ይድረሳቸው፡፡ በዚህ ጽሑፌ የምናገረው በእውነት ለቤተክርስቲያን ለሚጨነቁ ምዕመናንና አገልጋዮች ብቻ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ላለፉት ሃያ አንድዓመታት በታላቅ ፈተና ውስጥ አልፋለች፡፡ አሁንም እያለፈች ነው፡፡ እግዚአብሔር አይበለውናምናልባት የከፋው ፈተና ያለው ከፊት ለፊታችን ሳይሆን አይቀርም፡፡ የዚህም ሰበቡ ችግሮቻችንንበቅጡ ካለመረዳታችንና ከቸልተኝነታችን የመጣ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ለመሆኑ የቤተ ክርስቲያናችንችግሮች በተለይ በውጪው ዓለም ምንና ምን ናቸው?

አስታራቂ ጉባኤው መግለጫ አወጣ


(ደጀ ሰላም፤ የካቲት 13/2005 ዓ.ም፤ ፌብሩዋሪ 20/2013/ PDF)፦ በአባቶች መካከል የተፈጠረውን መለያየት ላማራቅና ዕርቅ ለማውረድ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ የቆየው የሰላምና አንድነት ጉባኤ ጉዳዩን አስመልክቶ መግለጫ አወጣ። የመግለጫው ምክንያት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ጉባኤ ላለፉት ሦስት ዓመታት በአገር ቤትና በውጭው ዓለም የሚገኙ አባቶችን በማስማማት ቤተ ክርስቲያንን አንድ ለማድረግ ያደረገውን ከፍተኛ ጥረት በዝርዝር ለመግለጽና የዕርቁ ሒደት ምን ይመስል እንደነበር በኢትዮጵያም ሆነ በመላው ዓለም ለሚኖሩ መላው ኦርቶዶክሳውያን ካህናት፣ ምእመናንና የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምርን እንዲያውቁት ለመግለጽ ነው” ያለው መግለጫ ዝርዝር ሐሳቦችን አካቷል። ሙሉ ቃሉን ከዚህ በታች ተመልከቱ።

Tuesday 19 February 2013

“ምርጫ ውስጥ ስካተት አትርሱኝ” አቡነ ጎርጎርዮስ


(አንድ አድርገን ህዳር 11 ቀን 2005 ዓ.ም)፡- “ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ፤ ክብር ፤ ባህል ፤ እምነት ፤ሥርዓት ፤ መንግሥትና ቋንቋ ያቋቋመች ፤ የማትናወጥ ከመሆኗ ጋር ፤ ከሔኖክ ፤ ከመልከ ጼዲቅ ፤ ከነቢያትና ከሐዋርያት የተላለፈውን ትምህርት ፤ ሥርዓት ፤ እምነት ከትውልድ ወደ ትውልድ ስታስተላልፍ የኖረች ፤ በማስተላለፍ ላይ ያለች ፍኖተ ሕይወት ናት፡፡ ቅዱሳን አበውን ፤ ኃያላን ነገሥታትን ፤ ልዑላን መሳፍንትን ፤ ክቡራን መኳንንትን ፤ ዐይናሞች ሊቃውንትን በሥጋ ፤ በነፍስ ወልዳ ያሳደገች የሌላ የማትፈልግ ፤ የራሷንም የማትለቅ ዕጥፍ እናት ፤ ስንዱ እመቤት ናት፡፡” በማለት ስለ ቤተክርስቲያን የተናገሩት ታላቁ ሊቅ የቀለም ቀንድ አለቃ አያሌው ታምሩ ነበሩ ፡፡ እንዲህ የተባለላት ቤተክርስቲያን  ዛሬ ከእርቀ ሰላም የተከደነ አጀንዳ በኋላ ስድስተኛ ብላ ፓትርያርክ ለመሾም ወሳኝ ጊዜ ላይ ትገኛለች፡፡ 

የአቶ መለስ ዜናዊ ሃውልት ሲመረቅ አቡነ ጳውሎስ ያረፉበት ቦታ እንደታጠረ ነው




(አንድ አድርገን የካቲት 12 ፤ 2005 ዓ.ም)፡- የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር የአቶ መለስ ዜና ሀውልት ትላንትና የካቲት 11 2005 ዓ.ም ባለቤታቸው ወ/ሮ አዜብ ፤ ቤተሰቦቻቸው እና ጥቂት ባለስልጣኖች በተገኙበት ተመረቀ ፡፡ በምርቃቱ ጊዜ አንድም የሚዲያ ተቋም በቦታው አልተገኝም ፤ የዲዛይንና የኤሌክትሪካል ስራውን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ ስራው የመከላከያና ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ድርጅት አማካኝነት የተሰራ ሲሆን ስራውን  ለማጠናቀቅ ከስድስት ወር በላይ መፍጀቱ ታውቋል፡፡ የአቶ መለስ ዜናዊ አስከሬን ያረፈበት ቦታ በመንበረ ጸባኦት ቅድሥት ሥላሴ ካቴድራል ግቢ ውስጥ በስተግራ በኩል  በግምት ከ260 እስከ 300 ካሬ ቦታ የፈጀ ሲሆን አስከሬኑ ያረፈበት ቦታ ከ40 ካሬ እንደማይበልጥ በቦታው ተገኝተን ለማወቅ ችለናል፡፡ ይህ ሃውልት ሙሉ በሙሉ በጥቁር እምነበረድ የተሰራ ሲሆን በምሽት የተለየ ውበት የሚሰጡት በርካታ መብራቶች ተገጥመውለታል ፡፡  ሃውልቱ ላይ “የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር አቶ መለስ ዜናዊ ከ1947-2004 ዓ.ም”የሚል ጽሁፍ ብቻ በአማርኛ እና በእግሊዝኛ ተጽፎበታል፡፡ ሃውልቱ ላይ ፎቶም ሆነ ሌላ ጽሁፍ አይታይበትም፡፡ ቦታው ተገኝተን እንደጎበኝነው ሃውልቱ ለህዝብ እይታ ክፍት የሆነ ሲሆን ቦታው ላይ ባሉት በአራት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ጥበቃ እየተደረገለት ይገኛል፡፡ በግቢ ውስጥ የሚገኙ በርካታ ሃውልቶች ፊታቸው ወደ ቤተክርስቲያኑ ያዙሩ ሲሆን የአቶ መለስ ሃውልቱ ግን  ፊቱን ወደ ውጭ በር አድርገው ሰርተውታል፡፡

Monday 18 February 2013

አባ ፓምቦ

ቅድስት ሜላኒያ ስለ አባ ፓምቦ እንዲህ አለችው "ገና መጀመሪያ ጌዜ ከሮም ወደ እስክንድርያ ስመጣ የእርሱን ቅድስና ሰምቼ እንዲሁም አባ ኤስድሮስ ስለ እርሱ ነገረኝና ከዚያም እርሱ ወዳለበት ወደ በረሃው ወሰደኝ። እኔም በሳጥን ውስጥ የታሸገ ሦስት መቶ (300) ወቄት ወርቅ ወሰድኩና የሚፈልገውን ያክል እንዲወስድ ለመንኩት። እርሱ ግን ከተቀመጠበት ሳይንቀሳቀስ ሰሌን እየታታ ባረከኝና "እግዚአብሄር ዋጋሽን ይሰጥሽ ዘንድ ፈቃዱ ይሁን" አለኝ። ከዚያም ረድኡን "ይህን ውሰደውና በሊቢያና በደሴቶች ለሚኖሩት ወንድሞች ለሁሉም አከፋፍላቸው፣ እነዚህ ገዳማት ከሌሎቹ ይልቅ ድሃዎች ናቸውና" አለው። በግብጽ ላሉት ግን  የእነርሱ መሬት የተሻለ ለምነት ስላለው ምንም እንዳይሰጥ አዘዘው።

እኔ ግን ስለ ስጦታዬ የበለጠ እንዲያከብረኝና እንዲያመሰግነኝ ተስፋ በማድረግ እዚያው ቆምኩ። ሆኖም ምንም ሲለኝ ስላልሰማው፣ አባ ውስጡ ምን ያህል እንዳለ ታውቅ ዘንድ 300 ወቄት ነው አልኩት። እርሱ ግን እራሱን እንኳ ቀና ሳያደርግ "ያመጣሽለት እርሱ፣ ልጄ ሆይ፣ መጠኑን የሚነግረው አያስፈልገውም። ተራሮችን የሚመዝን እርሱ የዚህን ወርቅ ክብደት የበለጠ ያውቀዋል። የሰጠሺው ለእኔ ቢሆን ኖሮ በእርግጥ መንገርሽ አግባብ ነበረ። የሰጠሽው ለእግዚአብሄር ከሆነ ግን የመበለቲቷን ሁለቱን ሳንቲሞች ያልናቀ እርሱ ያውቀዋልና መንገር አያስፈልግሽም" አለኝ። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ምንም ሳይታመም ቅርጫት እየሰራ እያለ በሰባ ዓመቱ ዐረፈ። ሊያርፍ ሲል እየሰራ የነበረውንና ሊያልቅ ትንሽ የቀረውን ቅርጫት ላከልኝ፣ እንዲህ በማለት፣ "ታስቢኝ ዘንድ በእጆቼ የተሰራውን ቅርጫት ተቀበዪ፣ ታስቢኝ ዘንድ የምተውልሽ ሌላ ምንም ነገር የለኝምና።" ስጋውን ለመቃብር ካዘጋጀው በኋላ ቀበርኩትና ከበረሃው ተመለስኩ። ያቺን ቅርጫትም እስከ ህይወቴ ፍጻሜ ድረስ በክብር አኖርኋት።

ይህ አባ ፓምቦ ሊሞት ሲል እንዲህ አለ ፦ "ወደዚህ በረሃ ከመጣሁበትና በአቴን ሠርቼ በዚህ መኖር ከጀመርኩበት ጊዜ አንስቶ በእጄ ያልሰራሁትንና ያልደከምኩበትን ነገር አልተመገብኩም፣ የምጸጸትበት ቃል አልተናገርኩም። ሆኖም ሃይማኖተኛ መሆን ገና ምንም እንዳልጀመረ ሰው ሆኜ ነው ወደ እግዚአብሄር የምሄደው።"

የአባታችን የአባ ፓምቦ ምልጃውና በረከቱ አይለየን። አሜን።

(ከበረሓውያን ሕይወትና አንደበት በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ)
ጥር 2003 ዓ.ም

ክርስቲያኑ ኢትዮጵያዊ መብቱን ለማስከበር ያልቻለባቸውና የማይችልባቸው ምክንያቶች


ይህ ጽሑፍ የአቅማቸውን ጥቂት ነገር ለማድረግ የሚተጉትን ላይመለከት ይችላል።

(ደጀ ሰላም የካቲት 8/2005፤ ፌብሩዋሪ 15/2012/ PDF)፦ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአገራችን በኢትዮጵያ እየተስፋፋ በመጣው እምነትን በነጻ የማራመድ መብት ገፈፋ ዋነኛ ተጠቂ ከሆኑት ኢትዮጵያውያን መካከል ኦርቶዶክሱ ክፍል ዋነኛ ተጠቃሽ ነው። በወታደራዊው የደርግ ዘመን የነበረውን ግፍና መከራ እንኳን ለጊዜው ብናቆየው “የሕዝብ ብሶት ወለደኝ” ያለው የኢሕአዴግ መንግሥት ከተመሠረተ ወዲህ ቤተ ክርስቲያናችን በዓይነ ቁራኛ ከመታየት እስከ የ“ነፍጠኛ ጎሬ” እስከመባል ድረስ ብዙ ዘለፋ አስተናግዳለች። ከዚያም ገፋ ሲል በአንዳንድ አክራሪዎች ምእመናኗ ታርደዋል፣ አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፣ ከየአካባቢው እንዲፈናቀሉ ተደርገዋል። ለዚህም በስልጣን ላይ ያለው ፓርቲ የሚያራምደው ፖሊሲ ሁነኛ ምክንያት ነው።