Sunday 18 May 2014

ዜና ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ: መዝሙር አለቀሰ

ዜና ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ: መዝሙር አለቀሰ

መዝሙር አለቀሰ

መዝሙር አለቀሰ
የያሬድ ዝማሬ፣ የአዘማመር ስልቱ
የበገናው ቃና፣ማሲንቆ ቅኝቱ
የከበሮው ውበት የዋሽንት ፍሰቱ፡


ነበር ተፈጥሯቸው ስብሐት ሊዘሩ
ሥርዓት ሊያከብሩ
መንፈስን አድሰው ውበት ሊደምሩ
ምህላ ሊያደርሱ ኑዛዜ ሊያወሩ
ስንዱዋ እመቤት ቤተ ክርስቲያን ቅድስት
እንዳላስተማረች ሁሉን በሥርዓት


ዛሬማ አፍ የፈታ ሁሉ እያንጎራጎረ፣
ቀኖና ትውፊቱን እየሸረሸረ
የመዝሙር ሥርዓቱ ስልቱ ተቀየረ
መዝሙር ዜማ ሳይሆን ጩኸት ሆኖ ቀረ
ለነፍስ ሐሴት ትቶ ለሥጋ አደረ


ሳኦልም ከደዌው እንዳልተፈወሰ
ወኅኒውም በመዝሙር እንዳልፈራረሰ
መዝሙር ቅዱሳንን እንዳላወደሰ
ዜማን ሐዘን ገባው መዝሙር አለቀሰ


ንጉሥ ገብረ መስቀል ጦር ከእግር ሰክቶ
በፍጹም ተመስጦ አለምን ረስቶ
እንዳልነበር ሁሉ ጸጋችን ምግባችን
መዝሙር አንገት ደፋ ከመላእክት በላይ አዋቂዎች ሆነን


ሳይጠፋ መዝሙሩ እስከ ሥርዓቱ
ፈር እየለቀቀ ዘማሪ ነኝ አለ ሁሉም በየቤቱ
በጠፋበት ሁሉ ተሰጥኦው መክሊቱ
መዝሙር አለቀሰ ተገፍቶ መብቱ
ተጥሶ ሥርዓቱ።
ምንጭ
ገድለ ቅዱሳን Gedle Kidusan Acts of Kidusan

Friday 16 May 2014

ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተ ክርስቲያን

መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ

ብዙዎች ኢየሱስ ክርስቶስን ቤተ ክርስቲያን እንደማትሰብክ አድርገው ለማቅረብ ይሞክራሉ፤ ነገር ግን ሐዋርያዊት የኾነችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ስለክርስቶስ ያላስተማረችበት ጊዜ የለምም አይኖርም፤ ደግሞም እናት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በጊዜያችን አንዳንዶች መናፍቃን የኢየሱስን ክብር አሳንሰው ከአብ በታች አድርገው እንደሚያስተምሩት ሳይኾን በእውነት ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክብሩ የተካከለ፣ ቅድመ ዓለም የነበረ አኹንም ያለና ዓለምን አሳልፎ የሚኖር፤ ለፍርድ ዳግመኛ የሚመጣ፤ እውነተኛ ፈራጅ የአማልክት አምላክ የነገሥታት ንጉሥ ነው ብላ የምታስተምረው፡፡ ይኽ ብቻ ሳይኾን ሥጋውን ደሙን በምትሠዋበት በቃል ኪዳን ታቦቱም ላይ “ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው” (የሕያው የአብ የባሕርይ ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ) ብላ አክብራ ስሙን ትጽፋለች እንጂ በድፍረት ሆና ስሙን መቀለጃ አታደርግም፡፡

Monday 21 April 2014

ከትንሣኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ

በመቅደስ ተስፋዬ

ሰኞ- ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡

ማግሰኞ- ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29

ረቡዕ- አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡ 

ሐሙስ- አዳም ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡

አርብ- ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡

ቅዳሜ- ቅዱሳት አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡

እሁድ- ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡ -

መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንላችሁ -

Saturday 19 April 2014

ትንሣኤ ዘክርስቶስ - የክርስቶስ ትንሳኤ

ሦስት መዓልት እና ሦስት ሌሊት በመቃብር፤
ሦስት መዓልት እና ሦስት ሌሊት የሞላው እንዴት ነው?፤
እንዴት ተነሣ?
ለምን በአዲስ መቃብር ተቀበረ?
እንዴት በዝግ መቃብር ተነሣ?
መቃብሩን ማን ከፈተው?

(መልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው/ PDF):- ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስክርስቶስ ድኅነተ ዓለምን በመስቀል ላይ ከፈጸመ በኋላ በአካለ ሥጋ ወደ መቃብር ወረደ÷ ይኸውምበመቃብር ፈርሶ በስብሶ መቅረትን ሊያስቀርልን ነው፡፡ በአካለ ነፍስ ደግሞ ወደ ሲኦል ወረደ÷ይኸውም በሲኦል ለነበሩ ነፍሳት ነፃነትን ይሰብክላቸው ዘንድ ነው፡፡ መለኮት፥ በተዋሕዶ፥ ከሥጋምከነፍስም ጋር ነበረ፡፡ ለዚህ ነው፥ መቃብር ሥጋን ሊያስቀረው ያልቻለው፤ ሲኦልም ነፍስን ማስቀረትአልተቻለውም፡፡

Tuesday 15 April 2014

ከአንድ ፕሮቴስታንት እህታችን የደረሰን ጥያቄ

በአሸናፊ መንግስቱ

ኦርቶዶክሶች የዳናችሁት በክርስቶስ ሞት ሆኖ ሳለ በሞቱ ታዝናላቹ፤ ክርስቶስ ባይሰቃይ አትድኑም ነበር ስለዚህ በስቃዩ መደሰት ሲገባቸሁ ለምን ታዝናላቹ?

መልሱን በአጭሩ ለመመለስ ያህል :-በመዳናችን እንዲሁም በትንሣኤው እንጂ በሞቱ አንደሰትም! ለምን የሚለውን ለማወቅ ህሊና ብቻ ይበቃልና አንድ ቀለል ያለ ምሳሌ ሰጥተን እንመልከተው፡-


እጅግ በጣም ከሚወድህ ወዳጅህ ጋር አብረህ በመንገድ ላይ እየተጓዝህ ሳለ አድብቶ ይጠብቅህ የነበረ ጠላት መሳሪያ አውጥቶ ወዳንተ ይተኩሳል ልብ በል መሳሪያው የተተኮሰው ላንተ እንጂ ለወዳጅህ አይደለም መሳሪያው ካገኘህም ያለጥርጥር ትሞታለህ ነገርግን ወዳጅህ ካንተ ቀድሞ የመሳሪያውን መተኮስ አይቶ ነበርና ደረቱን ሰጥቶ ከፊትህ ቆመ መሳሪያውም ደረቱ ላይ አረፈችና ወዳጅህ ስላንተ ሞተ፤ አንተን አድኖ ሞተ፤ አሁን አንተ በህይወት ያለኸው ወዳጅህ ስለሞተልህ ነው፡፡

እናማ አሁን አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ አንተ የምትደሰተው በወዳጅህ መሞት ነው ወይስ በመዳንህ? መቼም ወዳጄ ለኔ ሲል ሞቷልና ሞቱ ያስደስተኛል ካልክ አንተ ጠላቱ እንጂ ወዳጁ አይደለህም ከምንም በላይ ደግሞ ራስ ወዳድ መሆንህን ያሳያል፡፡ እኛ ግን በወዳጃችን ሞት እናዝናለን፤ በህይወት ስለመኖራችን ደግሞ እንደሰታለን፤ ወዳጃችን ስለኛ ስለተቀበለው ህመም፤ ስላቃሰተው ማቃሰትም በዘመናችን ሁሉ እያሰብነው እናዝናለን፤ በዚህም ወዳጃችን ለእኛ የከፈለውን ዋጋ ማወቃችን ይገለጻል::

አባቶቻችን እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ጥበብ ይልቅ ዓለምን ያዳነበት ይበልጣል እንዲሉ ነገሩን ቀለል አድርጎ ለማሳየት እንጂ ይህ ምሣሌ በምንም አይነት የክርስቶስን የማዳን ጥበብ አይገልፅም፡፡

እንግዲህ ለሥጋዊ ወዳጃችን እንዲህ ካዘንን አንዳች ኃጢያት ሳይኖርበት ስለተንገላታው ስለክርስቶስ ስቃይ እንዴት አናዝን? የእርሱን ግርፋትና መንገላታት እያሰበ ስለማልቀስ ፋንታ የሚስቅስ እንዴት ያለ ኃጢያተኛ ነው? የእርሱን መቸንከር እያየ ያለኃጢያቱ የማይሞተው ሲሞት እየተመለከተ ስለማዘን ፈንታ የሚደሰትስ እንዴት ያለ ክርስቲያን ነው? በስቃይ የሚደሰትስ እንዴት ያለ ሰው ነው?

የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት መዳኛችን እንደሆነ እናምናለን ነገር ግን ስለመዳናችን እንደሰታለን እንጂ ስለስቃዩና ስለሞቱ ግን አብዝተን እናዝናለን ዳግም ደግሞ በትንሣኤው ታላቅ ሀሴትን እናደርጋለን፡፡

እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የቀደመችው እውነተኛይቱ መንገድ!!!!

‹‹ሰሙነ ሕማማት››


በዲ/ን ህብረት የሺጥላ
‹‹ሰሙነ ሕማማት›› መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓት ነው፡፡ በርካታ ሰዎች ቤተ ክርስቲያንን ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ የምትጓዝ አካል አድርገው ሊገልጧት ይሞክራሉ፡፡ ይህ እጅግ አላዋቂ መሆናቸውን ይመሰክራል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከመጽሐፍ ቅዱስ ያልተገኘና በሥጋዊና በደማዊ ዕውቀት ላይ የተመሠረተ ሥርዓት የላትም፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ‹‹ከሕማማቱ በኋላ›› በማለት ስለ ሰሙነ ሕማማት የሚያወሳ ቃል ተጠቅሟል፡፡ (የሐዋ1.3) ሰሙነ ሕማማት የሁለት ቃላት ጥምር ውጤት ነው፡፡ ‹‹ሰሙን›› የሚለው ቃል ‹‹ሰመነ›› ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ስምንት ቀኖች ወይም ሳምንት ማለት ነው፡፡ ‹‹ሕማማት›› የሚለው ቃልም እንደዚሁ ‹‹ሐመመ›› ወይም ‹‹ሐመ›› ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን መከራዎች ማለት ነው፡፡ ‹‹ሕማማት›› የምንለው ለብዙ ሲሆን ነው፡፡ ለአንድ ወይም ለነጠላ ሲሆን ደግሞ ‹‹ሕማም›› እንላለን፡፡ እንግዲህ ሁለቱን ቃላት በማናበብ ‹‹ሰሙነ ሕማማት›› ስንል ‹‹የመከራዎች ሳምንት›› ማለታችን ነው፡፡

በግብረ ሕማማት ውስጥ የሚነገሩ ባዕድ ቃላት


Saturday 12 April 2014

አዎ ማኅበረ ቅዱሳንን ተጠንቀቁ! ትልቁ ስጋት እሱ ነውና


በአዲሱ ተስፋዬ

መነሻ

ይህንን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ሰንደቅ ጋዜጣ በሚያዝያ 1/2006 ዓ.ም እትሙ ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ያወጣው ቃለ መጠይቅና ሀተታ ነው [i] :: ሶስቱም አስተያየት ሰጭዎች “ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ነው:: ስለዚህም መንግስት ሊያፈርሰው ነው ” የሚለው ወቅታዊ ዜና ምንጩ ከየት እንደሆነ ግልጽ እንዳልሆነ ጠቅሰዋል :: በፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አበበ ወርቁ ጉዳዩን “በሬ ወለደ ነው” ብለው ሲያጣጥሉት ፣ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ደግሞ ” የዚህ ወሬ ምንጩ ከየት እንደሆነ አናውቅም” ሲሉ ተመሳሳይ ነገር ተናግረዋል።

Wednesday 2 April 2014

የጎልማሶችና ወጣቶች ማኅበራት ኅብረቱ በቤተ ክርስቲያን ስም የሚፈጸሙ ሕገ ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር መዘጋጀቱን አስታወቀ፤ በወጣቶቹ ዝግጅት የተደናገጡ የለውጥ ተቃዋሚ አማሳኞች የኅብረቱን እንቅስቃሴና አመራሮቻቸውን በሽብር ለመወንጀል እያሤሩ ነው

ቁጥጥር ከሚደረግባቸው ሕገ ወጥ ተግባራት መካከል÷ ያልተፈቀደላቸው ሰባክያን ስምሪትና የኅትመት ውጤቶቻቸው ሽያጭና ስርጭት፣ የአስመሳይ ባሕታውያንና መነኰሳት ነውረኛ ድርጊቶች፣ ሕገ ወጥ ልመና፣ የአጥቢያ አስተዳደር ሙስናና የወጣት ሱሰኝነት ይገኙበታል፡፡
ማዕተብ ያለው ኦርቶዶክሳዊ ምእመን በተለይም ወጣቱ ከሱስ ነጻ መኾን አለበት፤ መስቀሉን አንጠልጥሎ በየባንኮኒውና በየዳንኪራው ከመታየት መጠበቅ አለበት፤ ዶግማውን፣ ቀኖናውንና ትውፊቱን ያወቀና የጠነቀቀ፣ በኢኮኖሚያዊና ፋይናንሳዊ አቅሙም ጠንካራና እርስ በርሱ መደጋገፍ ይገባዋል፡፡
102 ያኽል ማኅበራት አንድነት የፈጠሩበትና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አቅራቢነት የቅ/ሲኖዶሱን ዕውቅና ያገኘው ኅብረቱ ከ150,000 በላይ አባላት አሉት፡፡ የኅብረቱ አመራሮችና አባላት፣ ወቅቱ ከሰንበት ት/ቤቶች አንድነትና ከማኅበረ ቅዱሳን ጋራ በፍቅር እስከ መጨረሻው የምንቆምበት ነው ብለዋል፡፡
‹‹ቤተ ክርስቲያን ተጨንቃ ትጣራለች፤ የምትጣራው ወጣቱን ነው፤ ወጣት ዕውቀትና ጉልበት አለው፤ እኔ ሴቷን ጨምሮ ኹላችን እያንዳንዳችን ሓላፊነት አለብን፤ ወይ ግዴታችሁን ተወጡ ወይ ውረዱ የምንልበት ወቅት ነው!!›› /የማኅበራት ኅብረቱ ሰብሳቢ ወ/ሪት ፌቨን ዘሪሁን/

(ኢትዮ – ምኅዳር፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፷፪፤ መጋቢት ፳፬ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.)