Friday 12 October 2012

የቃለ ዓዋዲው ማሻሻያ ረቂቅ ይመከርበት!


መስከረም 30 ቀን 2005

ሰበካ ጉባኤ በካህናትና በምእመናን ኅብረት ላይ የቆመ መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደራዊና መዋቅራዊ ሥርዐት ነው፡፡ ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ባሉት መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ በየደረጃው አመራር ይሰጣል፣

መስኪድ የሚያሰሩት ሚኒስትር


  • አቶ ጁነዲን ሳዶ በእናታቸው ግቢ በአርሲ ሁሩታ አርብ ገበያ አካባቢ መስኪድ እያሰሩ ነበር
(አንድ አድርገን ጥቅምት 2 2004 ዓ.ም)፡- ከሳምንታት በፊት “ቀይ መብራት” በሚል  ጽሁፍ በአሁኑ ሰዓት ሃይማኖትን ተገን አድርገው ስለሚሰሩ ስራዎች ትንሽ ለማስዳሰስ መሞከራችን የሚታወቅ ነው ፤ ብዙዎች ህዝብ የጣለባቸውን ሃላፊነት በአግባቡ በመወጣት ስራቸውን በአግባ የሚሰሩ ብዙ ባለስልጣኖች እንዳሉ ሁሉ በርካቶች ደግሞ ህዝብና መንግስት የጣለባቸውን ሃላፊነት ወደ ኋላ በማለት ለሚከተሉት ሃይማኖታቸው ቅድሚያ በመስጠት በርካታ ስራዎች መስራታቸው ይታወቃል ፤ ከነዚህ ሰዎች አንዱ በአሁኑ ጊዜ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ኃላፊ አቶ ጁነዲን ሳዶ አንዱ ናቸው ፤ አቶ ጁነዲን ሳዶ ተወልደው ያደጉበት ቀዬ በአርሲ ክፍለ ሀገር ሁሩታ አርብ ገበያ  የገጠር አካባቢ መሆኑ ይታወቃል ፤ እኝህ ሰው በስልጣን በነበሩበት በርካታ ዓመታት በአካባቢያቸው ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ጥቂት መስኪዶችን አስገንብተዋል ፤ በቅርቡ በእናትና በአባታቸው የመኖሪያ ግቢ ውስጥ ትልቅ መስኪድ እያስገነቡ መሆናቸው ይታወቃል ፤ ይህ መስኪድ በሚሰራበት ወቅት ከዋናው የገጠር መንገድ ወደ መስኪዱ ልዩ መንገድ እንዲሰራ ከፍተኛ ግፊት ያደርጉ እንደነበር የቅርብ ሰዎች ይናገራሉ ፤ በኦህዴድ ውስጥ ስራ አስፈጻሚ በመሆን እያገለገሉ የነበሩት አቶ ጁነዲን ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመጠቀም በቅርቡ መንግስት እርምጃ ወስዶባቸዋል ፤ ከ2 ወር በፊት የመንግስት ልዩ ሃይል እኚህ ሰው ላይና በዙሪያቸው የሚገኙ ሰዎች ላይ ባደረገው ልዩ ክትትል ወንጀል አግኝቶባቸዋል፡፡