Friday 13 December 2013

....የይሁዳ ሰላምታ የቀሪ ሒሳብ ማስተካከያ ነው!!


ከብርሃን ብሂል
ከፌስቡክ ገጿ ላይ የተወሰደ

ሰሞኑን ከሀዋሳ ንፋስ ማዶ አንድ ወሬ ሰማን እነ……….ይቅርታ ጠየቁ አሉii
ማንም ሰው ስለበደሉ ይቅርታ መጠየቁ አጀብ የሚያሰኝ የሚያስመሰግንም ነው፡፡ ስንፀልይም “…..የበደሉንን ይቅር እንደምንል….. እንል የለ? ግን የሰዎቹ ጥፋት የሰው ነው ወይስ የሃይማኖት?(ሰዎቹ የበደሉት የሀዋሳን ምእመን ነው ወይስ ሃይማኖታችንን)? ታዲያ የሃይማኖት በደል በጉልበት(በሰዎች ፊት) በመንበርከክ ይቅርታ ይባላል እንዴ? የሰው በደልስ ቢሆን ልብ ካልተንበረከከ ጉልበት ቢንበረከክ ምን ዋጋ አለው፡፡ የሃይማኖት በደል ግን በኃያሉ በእግዚአብሔር ፊት እራስን አዋርዶ በንስሃ በመመለስ፣ በቀኖና ቤተክርስቲያን፣ በእግዚአብሔር ቃል…. ሂድና እራስህን ለካህን አሳይ…. እንጂ፡፡