Thursday 5 July 2012


ቤተ ክርስቲያን “ተራሮችን አንቀጠቀጥኩ” በሚለው ወይም በ“ያ ትውልድ” ቁጥጥር ሥር፦ የዳላስ ተሞክሮ


(ደጀ ሰላም፤ ሜይ 20/2010)፦ ይህ ጽሑፍ በቅርቡ በተከታታይ ስናስነብባችሁ እና በዩ-ቲዩብም ስናሳያችሁ የቆየነው “የዳላስ ቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ተከታታይ” ሳይሆን ከዳላሱ ጉዳይ በመነሣት የቀረበ አጠቃላይ ምልከታ ነው። ርዕሱን የበለጠ ለመረዳት ግን ሁለት መሠረታዊ አባባሎችን መገንዘብ ያስፈልጋል። እነዚህም “ተራሮችን ያንቀጠቀጠ” እና “ያ ትውልድ” የሚሉት ሐረጎች ናቸው። እነዚህ ሁለት ወካይ ሐረጎች አሁን ኢትዮጵያን በመምራት ላይ የሚገኘው የኢህአዴግ እና የኢህአፓ መታወቂያዎች ናቸው። ኢሕአዴግ ስለ ራሱ ገድል ያወጣቸው የነበሩት (የነተስፋዬ ገብረ አብ) መጻሕፍት የሚታወቁት “ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ” በሚል ሲሆን ስለ ኢሕአፓ ታሪክ በሰፊው ያተተው የፓርቲው መሥራች ክፍሉ ታደሰ የጻፋቸው መጻሕፍት ደግሞ “ያ ትውልድ” ይባላሉ። ይህ ጽሑፍ እነዚህ ሁለት ትውልዶች ከቤተ ክርስቲያን ላይ እጃቸውን እስካላነሱ ድረስ በአገር ውስጥም ሆነ በውጪ ያለችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ነጻነት እንደሌላት ለማጠየቅ ይሞክራል።

ቤተ ክርስቲያን እኛ ልጆቿን ከኃጢአት ባርነት ነጻ ያወጣች፣ በእናትነቷ ደግሞ እኛን የወለደች እና በሰማያዊ ጸጋ ያሳደገች፣ በአገርነቷ ያሉንን መንፈሳዊና ዓለማዊ ቅርሶች የለገሰች ናት። ይሁን እንጂ ይህች ታላቅ ቤተ ክርስቲያን እርሷ ነጻ ባወጣቻቸው ልጇቿ የባርነት ቀንበር ሥር የምትገኝ “ገባር” ናት። በአገር ቤት በኢሕአዴግ ቁጥጥር ሥር፣ በውጪው ዓለም ደግሞ በአብዛኛው በተቃዋሚዎች ቁጥጥር ሥር የምትገኝ፤ በዚህም ሆነ በዚያ የራሷ ድምጽና አንደበት የሌላት ቤተ ክርስቲያን ናት። በተለይም ኮሚኒስታዊው የአብዮት ማዕበል በአገራችን ከነፈሰበት ከ1966 ዓ.ም (1974) ወዲህ ወታደራዊው የመንግሥቱ ኃ/ማርያም አገዛዝም ሆነ ሌላኛው ኮሚኒስታዊው የመለስ ዜናዊ አስተዳደር ከቤተ ክርስቲያን ጫንቃ ላይ አልወረዱም። በውጪው ዓለም ደግሞ ከኮ/ል መንግሥቱ ጋር የነበሩ፣ ወይም በአጼው ዘመን በከፍተኛ ሥልጣን ላይ ይገኙ ነበሩ እና ዘር ቆጣሪ ዘመዶቻቸው፣ ወይም ኢሕአፓ እና ኢሕአፓን መሰል ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች ቤተ ክርስቲያንን ተቆጣጥረዋል። እንግዲህ “እናንት ልጆቿ እባካችሁ ለእናታችሁ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ነጻነቷን መልሱላት፣ ከቀንበራችሁ አሳርፏት፣ የከበደ መዳፋችሁን አንሱላት” ስንል ሁሉንም ወገን ማለትም በአገር ውስጥ ያለውንም በውጪው ዓለም ያለውን የዳላስ ሚካኤሉንም ዓይነት አገዛዝ ማለታችን ነው።

በአገር ውስጥ
በአገር ውስጥ ያለው የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር በቀጥታም ሆነ ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ በኢሕአዴግ ፓርቲ ቁጥጥር ስር የወደቀ አስተዳደር ነው። ከቅ/ሲኖዶሱ ድምጽ ይልቅ የፓርቲው ድምጽ የበለጠ ተሰሚነት አለው። ሌላው ቀርቶ በዚህ ሳምንት መጨረሻ በሚደረገው አገራዊ ምርጫ ላይ አባቶች ምን ማድረግ እንደሚገባቸው መመሪያ እስከመስጠት የሚደፍር “ደፋር” ፓርቲ ያለበት አገር ነው። ቤተ ክህነቱም የመንግሥትን ድምጽ እየተከተለ “አብ ሲነካ ወልድ ይነካ” እያለ “መንግሥትን የሚነካብኝን ሥጋውን ለመከራ ነፍሱን ለሰይጣን” እስከማለት እንዲደርስ ያደረገ ፓርቲ ነው። በየትኛውም የቤተ ክህነቱ እንቅስቃሴ ውስጥ የመንግሥት ሚጢጢ ካህን-መሰል ካድሬዎች ተሰግስገውበታል። እውነቱን ለመናገር ኢህአዴግ ቤተ ክህነቱን የሚንቀውን ያህል ቤተ ክርስቲያኒቱን ደግሞ በእጅጉ ይፈራታል። ጥርስ እንደሌለው አንበሳ የሚመለከታትን ያህል እንዳሸለበ አንበሳም ይፈራታል። አንድ ቀን ብትነሣ ጉዴን ታፈላዋለች ብሎ ይሰጋል። ስለዚህም በዘር ላይ በተመረኮዘው ወገንተኝነቱ “ዘመኑ የነ እንትና ነው” የሚሉ ደቀ መዛሙርቱን በማሰለፍ በአባቶችና በአገልጋዮች መካከል ወደፊትም ሊያመረቅዝ የሚችል ጠባሳ በመጣል ላይ ይገኛል።

በውጪ አገር
በውጪው ዓለም ያለው የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በአብዛኛው በተቃዋሚ ፓርቲዎች የተጠለፈ ነው ማለት ይቻላል። በኢትዮጵያ ኢህአዴግ የሚውልባትን ግፍ፣ በውጪው ዓለም ደግሞ ሌሎቹ ፓርቲዎች እየደገሙት ነው።  አብዛኞቹ ካህናት የእነርሱን ፖለቲካ እንዲደግፉ፣ ባይደግፉም አፋቸውን ይዘው ቁጭ እንዲሉ ያስገድዳሉ። በዐውደ ምሕረቱ የፖለቲካ ማስታወቂያቸውን ይናገራሉ፣ ውግዘታቸውን ያስተላልፋሉ፣ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ይጥሳሉ። ለእነርሱ የማይገዙ ካህናትን አዋርደው ያባርራሉ። የሚቃወማቸውን በሙሉ “በወያኔነት” ፈርጀው ስሙን ያጠፋሉ። ከዚህም አለፍ ሲል ደግሞ ለራሳቸው እንዲመቻቸው ባደረጉት እና “ስደተኛ ሲኖዶስ” ባሉት ተቋም አማካይነት ለቤተ ክርስቲያን ትምህርት የማይታዘዙትን፣ ከአገር ቤት በተለያየ የሃይማኖት ችግር የኮበለሉትን፣ ሥነ ምግባርና ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት የሌላቸውን በጉያቸው አቅፈው ይኖራሉ።

በውጪ ያለው የቤተ ክርስቲያን ስብጥር ገለልተኛ፣ ስደተኛ እና የአባ ጳውሎስ  በሚል ኢ-ክርስቲያናዊ አከፋፈል የተቧደነ ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን ለዛና ወዝ ምጥጥ ብሎ ጠፍቶ ሃይማኖተኛው በፖለቲከኛው እግር ስር ወድቆ የሚገኝበት ሁኔታ ሊፈጠር በቅቷል። በዚህም ምክንያት ሥርዓት-አልበኝነት በመንገሱ ክህነት የሌላቸው “ክህናት”፣ ኦርቶዶክሳዊ ያልሆኑ ቦርዶች፣ የኑፋቄ ትምህርት የሚያስተምሩ ሐሰተኞች ተቀላቅለው ሃይ የሚባልበት ቦታ ጠፍቶ ሁሉም ተተረማምሷል። አንድ ሰው በሚያጠፋው ጥፋት ተጠያቂ የማይሆንባት ባለቤት አልባ ቤተ ክርስቲያን እየተፈጠረች ነው። በዳላስ ሚካኤል እየሆነ እንዳለውና በሌሎችም ቦታዎች እንደሆነው ባለቤት ስለሌላት ጉዳያችን በሙሉ ወደ ፍርድ ቤት እየሄደ መሳቂያ እና መሳለቂያ ሆነናል። የፖለቲካና የግል ጥቅም ዓላማ እንጂ ሌላ ግብ የሌላቸው፣ በቅጡ ከሲጋራ ሱሳቸው እንኳን ያልተላቀቁ፣ በሥርዓት በቤተ ክርስቲያን ጸሎት የማይሳተፉ፣ እምነቷን የማያከብሩ ነገር ግን አስተዳደሯን የተቆጣጠሩ “ቦርዶች” ታላቂቱን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ወደ ገደል እየመሯት ነው።


ምን ይሻላል?
የዚህ ችግር መኖር ገና ዛሬ ለእኛ የተገለጠ አዲስ “መገለጥ” አይደለም። ችግሩ የገባቸው ብዙዎች ናቸው። ይሁን እንጂ ገና አንገታቸውን ቀና ሲያደርጉ “ወያኔዎች ናቸው፣ ቅንጅቶች ናቸው፣ ቤተ ክርስቲያናችንን ለአባ ጳውሎስ (ለአባ መርቆርዮስ) ሊሰጡብን ነው፣ ጎበዝ ተነሥ፣ ማህበረ ቅዱሳን ናቸው፣ አድሃሪዎች ናቸው” እያሉ አንድም ሃይማኖታዊ ነጥብ በሌለው ክስ ስሙን ያጠፉታል።

መፍትሔው አጭር ነው። የቤተ ክርስቲያንን ለቤተ ክርስቲያን፣ የፖለቲካን ለፖለቲካ። በየቡድኑ ተቆርቁዳችሁ የተቀመጣችሁ እና የቤተ ክርስቲያናችሁ ጉዳይ የሚያስጨንቃችሁ አበው ካህናት፣ ምእመናን ቤተ ክርስቲያቱን ከዚህ ዓይነቱ አሳፋሪ ሸክም ልንገላግላት ይገባናል። ለዕለት ጉርስ ብላችሁ አፋችሁን የከደናችሁ፣ ዓይናችሁን የሸፈናችሁ ብትኖሩም ቢያንሰ በጸሎት ልትረዱ ይገባል። ለጊዜያዊ ጥቅም ብላችሁ የቦርድ ወይም የመንግሥት ሰባክያን የሆናችሁ ሰባክያነ-ቦርድም/ ሰባክያነ-ፖለቲካ ከታሪክ ተወቃሽነት ራሳችሁን ማዳን ይገባችኋል። በአገር ቤት ያለው የመንግሥት ከባድ እጅ ከቤተ ክርስቲያናችን ላይ እንዲመነሳ አጥብቀን የምንጮኸውን ያህል በውጪ አገርም ያለው እንዲስተካከል መጮኽ ይኖርብናል። እባካችሁ ለቤተ ክርስቲያን ነጻነቷን መልሱላት!!!


ቸር ወሬ ያሰማን፣ አሜን

27 comments:

Anonymous said...
sometimes, I thought something like this- we have take forceful action. we have to punish those who are playing a game on the church whether papas or mi'emen.
One day a courageous man shold do this.
Anonymous said...
i support your idea for the first time. this is independant mind. I love it and i will support it.
selamawi said...
በስመ ስላሴ አሃዱ አምላክ አሜን


ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባበራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፥10

መለያየትን የሚያነሣ ሰው ጠማማ እንዲሆን በራሱም ላይ ፈርዶ ኃጢአትን እንዲያደርግ አውቀህ፥ አንድ ጊዜ ሁለት ጊዜም ከገሠጽኸው በኋላ እንዲህ ከሚመስል ሰው ራቅ።

ወደ ቲቶ 3 10፥11

ይህንም እላለሁ። እያንዳንዳችሁ። እኔ የጳውሎስ ነኝ፥ እኔስ የአጵሎስ ነኝ፥ እኔ ግን የኬፋ ነኝ፥ እኔስ የክርስቶስ ነኝ ትላላችሁ።

1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፥12

ከላይ የቅዱሱን የእግዚአብሔር ቃል ለማስታወስ እንደሞከርኩት ቤተክርስቲያናችን የምትሰብከው እውነተኛው መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል እኛ ማን እንደሰበከንም ማወቅ የተሳነን ይመስለኛል እባካችሁ ሰዎችን አንመልከት በቃሉ ብቻ እንመራ ሰዎች በሚዘረጉት መንገድ አንጓዝ እግዚአብሔርን ብቻ እንከተል እውነቱ የት እንዳለ እያወቅን ለስጋዊ ጥቅምና ለዘረኝነት ቦታ አንስጥ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እንደሆነች ምንጊዜም ንጽህት ናት ብናጠፋ ብንበድል እራሳችን እንጠፋለን እንጅ ቤተክርስቲያንን አንጎዳትም ስለዚህ ለሰላምና ለይቅርታ ልባችንን እንክፈት የሰላም አምላክ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ይቅርታዉን እና ምህረቱን ያውርድልን ወስብሃት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመሰቀሉ ክቡር አሜን ,,,
Anonymous said...
Dear Dejeselam,
You are a living evidence for the inevitable freedom of our beloved church from the tribal thugs, the day time robbers, the taxi driving and parking lot bandits, the ehapa derg & woyane murderers who have been hell bent all along to disrupt, weaken and control the church so that they can spearhead their futile political agenda which usually is designed to oppress the peace loving people and pillage the country Ethiopia. I was hoping that one day Mahiber Kidusan to liberate the church from the stranglehold of the poisonous and parasite Ethiopians, unfortunately it seems that the Mahiber is spineless, dangerous, wicked, and righteous all at once just like the Lucifer. Therefore, the key lies in the hands of independent minded Ethiopians, which i thing the editor/s of this blog sphere rightly represents. Please, use it wisely.
Anonymous said...
ደጀ ሰላምን

ገና ዛሬ ቁም ነገርና ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን የወገነ ሀሳብ ስታቀርብ አገኘኋት ::

የእኛ ችግራችን እኮ : ችግሩን በግልጽ እያወቅነው :
በቀጥታ ችግሩን ከመግለጽ ይልቅ : የራስን የቡድን ስሜት በሌላው ክፍል ላይ ለመጫን የሚደረገ ጨለምተኛነት ነው ::

እኔ ከምስማማባቸው ነጥቦች መካከል

1. በውስጥም በውጭም ያለችው ቤተ ክርስቲያናችን በፖለቲካኞች ስር መውደቋ

2. ይህን ክፍተት ተጠቅመው በውስጧ የተሰገሰጉት መናፍቃን እና ፀረ ቤተ ክርስቲያን/ሃይማኖት የሆነው አጥፊ ተግባራቸው ::

3. ዓላማ የሌላቸው እና ለጥቅማቸው ብቻ ያደሩ : ከዛም በላይ በአንድ እጃቸው መስቀል በሌላው እጃቸው የፖለቲካ መሳሪያ ያሆኑ : ካሕናት መበራከት ::

ሲሆኑ :

[u]ለዚህ ሁሉ ችግራችን መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስበው[/u]

በመጀመሪያ ደረጃ : በሁለቱ አባቶች (አቡነ መርቆሬዎስና ዐቡነ ጳውሎስ) እና በተከታዮቻቸው መካከል ያለው ቅራኔ የሚፈታበትን ሂደት ለማሳካት መረባረብ ::

ቤተ ክርስቲያኗ አንድ አስተዳደር መከተል ከጀመረች : ኃይሏን አሰባስባ :
. ከመንግስት ጣልቃ ገብንተ ራሷን ለመከላከልና
. በስጧ የተሰግሰጉ መናፍቅቃንን ነቅሶ ለማውጣት ትችላለች ::
Anonymous said...
ደጀ ሰላምን

ገና ዛሬ ቁም ነገርና ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን የወገነ ሀሳብ ስታቀርብ አገኘኋት ::

የእኛ ችግራችን እኮ : ችግሩን በግልጽ እያወቅነው :
በቀጥታ ችግሩን ከመግለጽ ይልቅ : የራስን የቡድን ስሜት በሌላው ክፍል ላይ ለመጫን የሚደረገ ጨለምተኛነት ነው ::

እኔ ከምስማማባቸው ነጥቦች መካከል

1. በውስጥም በውጭም ያለችው ቤተ ክርስቲያናችን በፖለቲካኞች ስር መውደቋ

2. ይህን ክፍተት ተጠቅመው በውስጧ የተሰገሰጉት መናፍቃን እና ፀረ ቤተ ክርስቲያን/ሃይማኖት የሆነው አጥፊ ተግባራቸው ::

3. ዓላማ የሌላቸው እና ለጥቅማቸው ብቻ ያደሩ : ከዛም በላይ በአንድ እጃቸው መስቀል በሌላው እጃቸው የፖለቲካ መሳሪያ ያሆኑ : ካሕናት መበራከት ::

ሲሆኑ :

[u]ለዚህ ሁሉ ችግራችን መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስበው[/u]

በመጀመሪያ ደረጃ : በሁለቱ አባቶች (አቡነ መርቆሬዎስና ዐቡነ ጳውሎስ) እና በተከታዮቻቸው መካከል ያለው ቅራኔ የሚፈታበትን ሂደት ለማሳካት መረባረብ ::

ቤተ ክርስቲያኗ አንድ አስተዳደር መከተል ከጀመረች : ኃይሏን አሰባስባ :
. ከመንግስት ጣልቃ ገብንተ ራሷን ለመከላከልና
. በስጧ የተሰግሰጉ መናፍቅቃንን ነቅሶ ለማውጣት ትችላለች ::
Atnatewos said...
Atnatewos

It is fantastic and very very true article.
- The 1960s generation is passing soon.Now stand the new generation with your new and energetic power.God will be with you.
- Learn from Abune Shinoda of Egypt coptic church.They were in the same problem some 10 years back.Now their church administrative and spritual problems are solved.Their only problem is extrem muslims attack.
- Both TERARA YANKETEKETE TIWLID and YA TIWLID actors shouldn't feel bad with the fact that is written here above.Becouse it is not difficult to think as if they did all just by thinking for their mother land-Ethiopia.But past exeperiance show us all failurity.So shoudl we continue in the same way? NO BIG NO!!!!!
- Pick up your visible and invisible hands from church.You will see all what you wish to see.Since all of us are under the hands of our Almight God, we all shall get our lessons according to our acts.
YE ABATOCHACHIN AMLAK YILEMENEN
AMEN
Atnatewos
Anonymous said...
I admire the content of the article,but for some reason, it lefe me with a feeling that I am being set up to accept someone's agenda in the end?

one of the remedies for most of the problems in the Ethiopian orthodox tewahedo chruch here and in Ethiopia is the lack of unity among her followers of the faith.
We need ot bring our church fathers and resolve their differences. One hugh shortcoming of this DejeSelam is the absence of this topic in its leading article/postings. As is the case in past postings, this article does not put forth the need for the unity of church fathers. I know it is not be mistake and it bothers me.

My other comment is that, it is a known fact that Mahebere kedusan plays a big role in the shaping of the church's current conditions in Ethiopia and aboard. Most of the blame pointed at the others groups in the article can fairly be pointed at this group. The case in point is the situation at Dallas Kidus Mikael. MK needs to learn there is victory in loosing xsome battles. Bemeshenf Mashenef ...
Anonymous said...
This article assumes that Woyane and EPRP are the forces that are damaging the health of our church. It streaches a bit further and gives them credit for the "Synod in Exile" ...

I admit that politically-driven Ethiopian have heavely affect the dynamics of the chruch. However, there are those of us, who are not Woyane and are not old enough to have been in EPRP? We see what we do not like at church. We object many activities done in our chruches in the name of the church. We do not like ot see those who put their group's abjective before that of the church, including Mahebere Kidusan. We would like members of MK to take part in many church affairs, but we also want them to stop some the dominance they want ot have in many church affairs.

We are not Woyane, EPRP, or Menafikan ... Do not forget to include our concerns in the next parts of your article. I have a feeling anyone who even wants to give constructive feedback to members of the group is seen as opponent. So, surprise me by not labeling me and my kinds as Menafik and admit some of the mistakes, take responsibility and share that with us.
tewodros said...
Are u kidding me!
Stop and analyze your history once , let’s go back to the 3rd century ,we find great bishop and great kings.Abune selam and king St.Ezana & king St.Sizana , starting from them we have been using the political power for our church benefit. Even before that the Ethiopian jandereba went to Jerusalem why one of the reasons is he was government trader.
All our fathers prioritize their religion from their political stage. So They used it all. We are all very gready ,selfish, illiterate ,in love with abroad , hate each other….generally we all prioritize this world zan our spiritual life.
I sent a message for many peoples saying “ which party’s idea is good for our church?” No body cares or nobody wants to say it to me. One thing I was sure no body knew for sure. Let me tell u one thing z protestants are already competing in this election as a party . What exactly were u saying ,<< z politics should leave us alone.>> My brothers u are sleeping. wake up and start z rite politics ,otherwise the others will rotate us as they like. I hope u know where that takes church. And … I am sorry to say it but it is painful truth. There will be no Ethiopian orthodox church soon.
May God be with us all.
tewodros said...
Are u kidding me!
Stop and analyze your history once , let’s go back to the 3rd century ,we find great bishop and great kings.Abune selam and king St.Ezana & king St.Sizana , starting from them we have been using the political power for our church benefit. Even before that the Ethiopian jandereba went to Jerusalem why one of the reasons is he was government trader.
All our fathers prioritize their religion from their political stage. So They used it all. We are all very gready ,selfish, illiterate ,in love with abroad , hate each other….generally we all prioritize this world zan our spiritual life.
I sent a message for many peoples saying “ which party’s idea is good for our church?” No body cares or nobody wants to say it to me. One thing I was sure no body knew for sure. Let me tell u one thing z protestants are already competing in this election as a party . What exactly were u saying ,<< z politics should leave us alone.>> My brothers u are sleeping. wake up and start z rite politics ,otherwise the others will rotate us as they like. I hope u know where that takes church. And … I am sorry to say it but it is painful truth. There will be no Ethiopian orthodox church soon.
May God be with us all.
elganan said...
እኔ ማጋነን ካለሆነ አገር ውስጥ ያለው ምንም አላረገም እንደውም ቤተክርስቲያን ራሶን ትቻል በማለት በተደጋጋሚ የሰብካል ግን እሚሰማ ጠፋ ለምሳሌ አንድወቅት ፃፃሳሳት መለስ ዜናዊ ጋር ገብተው ያላቸውን አውቃለሁ ስሩ ህዝበን አታወናብዱ ነው ያላቸው ግን ለዚህ ልተፈጠሩም አባቶቻችን በውነት ነው የምለው ምንም እንቅፋት የለም አየቸዋለሁግታየ ለማንኛውም መልካም
Anonymous said...
እግዚኣብሔር ይባርካችሁ ደጀሰላማውያን፡
ይህን የመሰለ ያላዳላ ትክክለኛ ጽሑፍ ማቅረባችሁ ብእውነት በጣም እናመሰግናችሁ ኣለን።
እውነትና ግንባር ኣይሸሸግም እንደሚሉ ኣበው፡
ያቀረባችሁ ኣስተያየት በጣም የሚደገፍና ሁላችንም ልናስብበት የሚገባን ጉዳይ ነው።
ግን ኣንዴ ላስታውሳጭሁ።
ቤተ ክርስቲያናችን የውስጥ ምስጥ የሆንዋት፡ ፖለቲኮኞች ብጃ ኣይደሉም።
ኣቡነ ጳውሎስና ኣቡነ መርቆሬዎስም ለብቻቸው ኣይደሉም።
እውነቱን ማወቅና መድኃኒት ልንፈልግለት የሚገባን ጉዳይ የማህበረ ቅዱሳን ጉዳይ ነው።
ይህ ማኅበር፡ ለቤተ ክርስቲያናችን፡ በጣም ኣደገኛ ስብስብ ነው፡ በዚህ ኣደገና ድርጅት ያልተሰደበ ጳጳስ። ፓትርያርክ፡ ካህን፡ ዲያቆን፡ ወጣት ኣለ ለማለት የሚቻል ኣይመስለኝም፡ የእነሱን ሓሳብና መንገዲ ያልተቀበሉ ሁሉ፡ መናፍቅ፡ ከሓዲ፡ ኦርቶጰንጤ፡ ተሓድሶ፡ ወዘተ የሚል ጥላሸት በመቅባት ስምን በማጉደፍ፡ እንደ ተዋጊ ቀንዳም በሬ፡ ከቤተ ክርስቲያን ያባረርዋቸውና ያጠፍዋቸው ኣማንያን ስፍር ቁጥር የላቸውም።
ከመናፍቃን ጋር፡ ገዥና ሸያጭ የተስማሙ ነው የሚመስለውን፡
ቤተ ክርስቲያናችን ሰላምን እንድታገኝ፡ ይህ ማኅበር ኣካሄዱን ተመልሶ መገምገምና ማረብ ኣለበት ባይ ነኝ።

በደሙ የዋጃትን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይጠብቅ ኣምላክ። ኣሜን
elganan said...
እኔ እምለው መኅበረቅዱሳን ያስወጣቸው እነ ማን ናቸው ? እባ ብእሴ አባ ዮናስ አባ ዘውዱ ስለዚህ እነዚህ እቤት ምቀመጥና ቤተክርስቲያንን መበጥበት ነበረባቸው? አልገባኝም ሰለማህበረ ቅዱሳን የሚነገረው ሲመስለኝ ማህበረ ቅዱሳንን የሚጠሉ ሰዎች ችግር ያለባቸው ይመስለኛል በተረፈ በተክርስቲያንን መጫወቻ ለማረግ ከልሆነ ማህበረ ቅዱሳንን መጥላት አያስፈልግም ወይም መቃወሚያችንን በትክክ እናሰቀምጥ እና ሁላችንም እንመን
Anonymous said...
Iam always surprized when I see comments against mahibere kidusan. Every thing people relates to MK? what do u think is the reason?why do not you see its true history and fruitful activities in the church.The only reason why most educated individuals across the country engaged to love EOTC is mainly because of MK's activities in the colleges and universities.I do not want to forget a very important contribution of sunday schools and few dedicated church fathers who want to the see the participation of the youth in church activities. pls let us think strategically than uttering here and there with out objectives.with regards to the above posted topic it quite true that politics tries to suppress our church's develpment and participation of is members in orgnising the church to make forward the way to liberyand freedom from earhly deeds. By the way the true democrate in the world is only Our Lord who gave us freedom to choose and live based on our free will.
may God give us our church chance to rise up again!
Anonymous said...
ይቺን የላይኛዋን አስተያየት የሰጠህ ወንድም ያልገባህ ነገር ያለ ይመስለኛል ::እነዚ ማሀበረ ቅዱሳኖች እኔ ሳውቃቸው ካገር ቤት ጀምሮ ጥሩ ሲሰሩ እንጂ ሲሳደቡ አላየሁም:: እንደውም ብዙ ተሃድሶና መናፍቆች ሲሰድቡዋቸው ዝም ማለታቸው ያናድደኛል :: እንዳንተ አይነቶቹም የሚሳሳቱት እነሱ ስለራሳቸው ስለማይናገሩ ይመስለኛል
ለማነኛውም ስራቸውን ለማየት ስትሞክር እውነቱን ታገኛለህ::

እንዲየውም ጌታ እነሱን ባያስነሳ ኖሮ ዛሬ መናፍቅ ሀገሪቱን በተቆጣጠረ ነበር ::
እረ እንዲየዉም ያበርታቸው!
elganan said...
እኔ የሚገርመኝ ጠላት በተነሳ ቁጥር ማህበረ ቅዱሳን ላይ መዛቱ አይቀሬ ነው እስቲ የምታወቁ ከሆነ የአባልነት መመዘኛውን ንገሩንገሩን ዎንድሞቸ እኔ ሳስብ አብሬ ማገልገል ይሰማኛል ስለዚህ ካወቃችሁ እርዱን ከላይ የሰጠሁት አስተያየት ምንም መልስ አላገኘም ናነው!!!
maki said...
የኢትዩጵያ ቤተክርስቲያን ችግር ያለፀሎት ያለ ጾም የሚፈታ አይደለም ሁሉም ለራሱ ጥቅም ሲል እንጂ ለቤትክርስቲያኗ አሰቦ በጐያዋ ያለ የለም በተለይ ጳጳሳት በሁለቱም ሲኖዶስ ጋር ያሉት፡፡ ለቤተክርስቲያኗ ቢያስቡ ኖሩ ቀኝ ባልተገዛች ሀገር ሁለት ሲኖዶስ ባልኖረ ነበር፡፡ በተለይ የሁለት ሲኖዶስ ጉዳይ ችግሩ ያለው በውጪ ሀገር ነው ኢትዩጵያ ውስጥ በሁለት ሲኖዶስ ምክንያት ምንም አልተቸገርም፡፡ ጳጳሳቶቾ ግን ውስጥን በሚበላ መልኩ ፖለቲከኖች፣ ካድሬዎች ፣ ሙሰኞች እና ዘረኖች ናቸው፡፡ እኔ በግሌ ውጪ ላላችሁ ኢትዩጵያውን የምመክረው አሁን የኢትዩጵያ ሕዝብ እየተከተለ ያለውን መንገድ እንድትከተሉ ነው ማለት ከምንም ነገር በላይ ቤተክርስቲያን ትበልጣለች ሌላው ሁሉ ትርፍ ነው ሰውም በሰው ይተከካል እናት ቤተክርስቲያንን ግን የሚተካት የለም የሰውን ነገር ተውት ቤተክርስቲያን የማምን ፖለቲከኛ ቤት አይደለምችም ማንም ፖለቲከኛ በቤተክርስቲያን መጠቀም የለም ምክንያቱም ቤትክርስቲያን በሰው ስትያዝ መሪዋን ሰው ስናደርግ የቤተርስቲያኗ ባለቤት መንፈስ ቅዱስ ይወጣል፡፡ ስለዚህ እኛ ቤተክርስቲያን ውስጥ ካሉት ሰዎች መሻል እንደውም መብለጥ አለብን ማንኛውም ሰው እኛ ካልተቀበልናቸው ቤተክርስቲያን ውስጥ የፈለጉትን የማድረግ መብት የላቸውም፡፡ ተባብረን ቤተ ክርስቲያናችንን አናጥፋ፡፡

የቅዱሳን አምላክ እ/ር ለቤተክርስቲያናችን ሰው ይላክልን አሜን
Anonymous said...
I have tried to written previously to your site. I have discovered that you are biased and not allow free idea be expressed. If you continuing barring comments that has truthful and factual the negative side of Maheber Kidusan, and you are not publish it. Why it is? How do you contributed for the organization that only you post the positive side alone. There is different website that moderated the ongoing issue of the Dallas Church as http://www.tadias.com and http://www.abugidainfo.com/amharic/ and other as well. You have also the actual website of the Church http://stmichaeleoc.org/ for a better understanding of the issue than yours one side story. For me you are serving only your group than all-Ethiopians. Open up
ደጀ-ሰላም said...
To the Anonymous above,

Yes, we moderate comments to fence out unethical people who have no decency of matured dialogue. Since you are not using any name, we could not know if you have previously written us or not. Still, you blamed us to be partisan but not substantiate your comments with evidence. If you think our reports are not fair and true, then challenge us. By the way, Deje Selam will continue to write on Dallas case in depth, with the will of God. It is time to defend our Church; nothing but the Church, so help us God.
Cher Were Yaseman,
DS Team
Anonymous said...
እኔ በእውነቱ ብዙም ነገሮችን ጠለቅ ብዬ ባላውቅም አንዳንድ ሰዎች የሚሰጡት አስተያየት ግን ይገርማል
በመጀመሪያ ደረጃ አባቶችን ታውቋቸዋላችሁ? በተለይ በኢትዮጵያ ያሉትን:: ልካችሁን ብታውቁ ጥሩ ነው ቢያንስ እዚህ ከምንጽፈው የሚበልጥ የአገልግሎትና የቅድስና ሕይወት አላቸው ሁላችሁም ይህን አታጡትም::ነገር ግን በድፍረት ለመሳደብ ትፈጥናላችሁ ጽድቅ በስድብ አይሰራም::
ezih ethiopia yaluten abatoch yetewesenutinim bihon awkachewalehu betikikil le K/BETEKRISTIYAN agelgilot yemifatenu nachew min albat egna yemanawkachew bizu negeroch sileminoru zim bilen negerochin bandefedifibachew melkam new elalehu.
yalutin chigiroch lemekref ende meftihe yemasibew
1. ezih blog lay asteyayet yeminisetim hone yeminaneb sewoch betikikil sile k/BETEKRISTIYan andinet kelib honen entseliy yetselotachinin waga GETA aynesanim ena
2. abatochin yeminikerb sewoch degmo yegil tikmachinin kemasaded yalutin chigiroch eske meftiheyachew bedenb discuss madreg. yihinin sil beteley huletuin kidusan abatochin yeminikerb sewoch(betsu'e wekidus Aba Paulosin ena Abune Merkoriyosin malete new).
3. kezih wichi K/Betkristiyanin lematfat yeminrwarwat sewoch degmo k/BETKRISTIYAN yetemeseretechiw BE KIRISTOS dem mehonun banzenega ena arfen quch binil degmo GETA lobona endiseten binteyikew. Keminim neger belay degmo melkam ayeseru yalu ye agelgilot mahiberatin yelele sim eyeseten yeminisadebewn binakom yetim silemanders.
4.be melkam agelgilot lay yalen degmo be agelgilotaachin yebelete binitega.
elalehu
Ye AMLAKACHIN cherinet ye EMEBETACHIN amalaginet ye KIDUSAN miljana tselot KIDIST BETEKRISTIYANIN and yadirgili
Amen
Anonymous said...
ewnet new yalachihut Egziabher yemisanew neger yelemina yihinin tiwlid weyi yilewutew weyim kebetekrstiyan gelel yadrgilin. Abetu ebakih siman,yegnan hatyat satimeleket netsa yehonech agerachin betachin hiywetachin tarikachin selamachin yehonech betekrstiyanachinin nets a awtalin akim yelenim akim hunen Amen
Fikirte A said...
In the name of the holy trinity one divinity amen!

Abetu! yezelalem abat, yeselam aleka medihane-alem kiristos hoy, weden fekiden balametanew zer eyetemekan andituan b/k lemafires yeminitatarewin wede libonachin melisen! lemiyalefew lemitefaw poletica, siltan, lemayazalik sigawi tikim bilen zelalemawituan tewahido kebizu akitacha leminiwegat hulu akimachin min yahil endehone bemitasayibet menged tastemiren timekiren zend enimatsenihalen! Libonachinin bezer-manzer, befikre niway ena be-tihibit tebtibo ye-yazewin telat diabilosin, kefitretat hulu akibirehe bemeretikat beazagnitu enatachin dingil mariam lekso ena milja arikilin!. Yemininafikewin selam, fikir ena andinte be-betihe tatsena zend enileminihalen!!!
Anonymous said...
Dselamoch selewent senger bezuochachen yamenale themawen sel mahbeher kidusan sayehone sele andet betkerstyanachen newena yehnenem le Abe Serake weldeselase be posta lakulachew yehe bedneb esachwen yemlktachwalena eske yekoyen.
Anonymous said...
መልካም፤ አንድ ጥያቄ እንድጠይቅ ይፈቀድልኝ።
አቡነ ጳውሎስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መሪ ናቸው፤ የጻፉት መጽሐፍ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ዕምነትና ዶግማ ነውን?
አቶ ክፍሉ ታደሰ የኢሕአፓ አመራር አባል የነበሩ፤ [አሁን ግን እርሳቸው ይወቁት]፤ አንድ መጽሐፍ ስለ ኢሕአፓ ቢጽፉ የኢሕአፓ መርሕ ነበረ ማለት ትንሽነት ነው። የምትተቹበት እውቀቱና ችሎታው ካላችሁ በኦፊሴል ያወጣውን ማኒፌስቶ {ፕሮግራሙን]፤ በየወቅቱ የሚያወጣቸውን አቋሙን ተቹ።
ባልና ሚስት ተጣልተው ሽማግሌ ምክንያታቸውን ሲጠይቃቸው፤ የሚሰጡት ምላሽ እርሱ ለወር ወጪ የሚሰጠን አይበቃኝም፤ እርሷ ስገባ ፊቷን ታጠቁርብኛለች ይሆናል መልሳቸው። ዋናው ምክንያት ግን ሌላ ነው። እናንተም ዋናውን ምክንያታችሁን ለአንባብያን ሸሽጋችሁ በማይሆን ምክንያት ምስኪኑን አንባቢ አታደናግሩ።
ክርስትና ዕውነት ነው ዕውነት መስክሩ። ዕውነቱን የማታውቁት ከሆነ ደግሞ ለመጻፍ አትቸኩሉ።
Anonymous said...
"Anonymous said...

Dear Dejeselam,
You are a living evidence for the inevitable freedom of our beloved church from the tribal thugs, the day time robbers, the taxi driving and parking lot bandits, the ehapa derg & woyane murderers who have been hell bent all along to disrupt, weaken and control the church so that they can spearhead their futile political agenda which usually is designed to oppress the peace loving people and pillage the country Ethiopia. I was hoping that one day Mahiber Kidusan to liberate the church from the stranglehold of the poisonous and parasite Ethiopians, unfortunately it seems that the Mahiber is spineless, dangerous, wicked, and righteous all at once just like the Lucifer. Therefore, the key lies in the hands of independent minded Ethiopians, which i thing the editor/s of this blog sphere rightly represents. Please, use it wisely.
May 21, 2010 6:08 AM "


Dear Editor (Blogger) of DejeSelam,

ከላይ፡በተመለከትው፡አስተያየት፡ላይ፡ያቀረብኩት፡
አስተያየት፡ለምን፡እስካሁን፡እንዳልወጣ፡ለመጠየቅ፡
ነው።ጽሑፌን፡እንዳይወጣ፡የሚያደርግ፡ምን፡ተገኘ
በት?!

መድኃኔ፡ዓለም፡ክርስቶስ፡ተዋሕዶ-ኢትዮጵያን፡
በምሕረቱ፡ይጎብኘን! አሜን።


ሳሙኤል፡ዘአሰቦት።
Anonymous said...
How do we correct the Churches abroad ? Is that taking them to under aba Paulos's administration? you said that it is under woyane's influence. So, what comes first? I think, getting rid of woyane, restore the Church's power and working with the churches should be the order. Aseemingly genuine commentary,but in essence a woyane's approach. What is the solution you think?

ርዕሰ አንቀጽ፡- የሀገሪቱን ሰላም ለማስከበር የቤተ ክርስቲያኒቱን ሰላም ማስከበር



(ደጀ ሰላም፤ ኤፕሪል 2/2011)፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለኢትዮጵያ ያበረከትችውን አስተዋጽዖ መዘርዘር ለቀባሪው እንደማርዳት ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተለይ ሕግና ሥርዓትን አውጥታ፤ ካህናትና ምዕመናን በአንድነትና በመከባበር የቤተ ክርስቲያኒቱን ሥርዓተ እምነት፤ ዶግማና ቀኖና እንዲጠብቁና እንዲያስጠብቁ፤ በልማትና በማኅበራዊ ጉዳዮች በሕብረተሰቡ ዘንድ መረዳዳትና መቻቻል እንዲኖር አድርጋለች፣ በማድረግም ላይ ትገኛለች። ይህም ለሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጓል።

ስት ቤተ ክርስቲያን እነዚህን ሁሉ ተግባራት ለዘመናት ስታከናውን የቆየችው በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ያለው መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረድ በመጠቀምና በማክበር ነው። ይህም አራር ለዘመናት ሳይፋለስ ቆይቷል። ይህንን ከሀገሪቱ ከ50% በላይ የሆነና በሚሊዮን የሚቆጠር ምዕመን ይዛ በሕግና በሥርዓት ባታስተዳድር ኖሮ የቤተ ክርስቲያንቱ ሰላም ብቻ ሳይሆን የሀገሪም ሰላም ሊደፈር እንደሚችል እሙን ነው። የቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረድ ለማስጠበቅ እና በቤተ ክርስቲያንቱ አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ለሚወሰኑ ውሳኔዎች ተፈፃሚነት የግ ከለላ በመስጠት በየጊዜው የነበሩት ነገታትና የመንግሥት  አካላት በቂም ባይሆን የበኩላቸውን አስተዋጽዖ አበርክተዋል።

ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት የቤተ ክርስቲያቱን ዶግማና ቀኖና ለማፍረስና ብቷንና ንረቷን ለመዝረፍ እንዲያመ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረዷን መጣስ እየተለመደ መጥቷል። እነዚህን ሕገ ወጥ ተግባራት ለመከላከል የቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ ጠባቂና ወሳኝ አካል የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ እና በየደረጃው ያሉ እውነተኛ የቤተ ክርስቲያን አመራር አካላት የሚወስኗቸው ውሳኔዎችና አመራሮች ተግባራዊ እንዳይሆኑ ብዙ እንቅፋቶች እያጋጠሟቸው ነው። ለዚህም እንደማሳያነት በቦሌ የቆመው የፓትያርኩ ሐልተ ስምዕ መፍረስና በሐዋሳ ሀገረ ስብከት በተፈጠሩ ችግሮች ላይ የተወሰኑት ውሳኔዎችን ለማስፈፀም ያለው ፈተና መግለፅ ይቻላል። ከዚህ አንጻር ስንመለከተው፦

1.      የቤተ ክርስቲያንቱን ዶግማ፤ ቀኖና እና ትውት ለማስከበር እና የቤተ ክርስቲያንን ብት እና ንብረት ከውድመትና ከዝርፊያ ለመታደግ ጥረት በሚያደርጉ አባቶች ላይ እየተደረገ ያለው ዛቻ፤ ጫና እና ማስፈራሪያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የሚገኝ ጉዳይ እንጂ የሚቀንስ ሆኖ አለመገኘቱ፤ ይህም ጉዳይመንግሥት  በሀገሪ የለም፤ ሕግና ሥርዓት አስከባሪ የለም፣ መንግሥት ለቤተ ክርስቲያኒቱ ደንታ የለውም”’ እስከኪባል ድረስ አድርሶታል።

2.     ባለፈው ዓመት በተደረገው በብፁዓን አበው ላይ የደረሰው ድብደባ፤ አፈናና ዛቻ የፈፀሙት ግለሰቦች ለፍርድ አለመቅረብና ሕጋዊ ቅጣት አለማግኘት ምዕመኑ በመንግሥት  ላይ ያለውን ተስፋ እስከመጨረሻው እንዲሟጠጥ አድርጎታል።

3.     በዚህ ዓመትም በጥቅምት ወር በተደረገው ጉባኤ ላይም ቢሆን ብዙ ብፁዓን አባቶች የማስፈራሪያ ዛቻዎች በስልክ እና በአካል ተሰንዝረዋል። አሁንም የቤተ ክርስቲያቱ ዶግማና ቀኖና እንዲጠበቅ፤ ብቷ እና ንብረቷ እንዳይዘረፍ፤ እና የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረድ እንዲጠበቅ በሚታገሉ አባቶች ላይ ከእነዚህ ቡድኖች የሚሰነዘረው ማስፈራሪያ ቢጨመ እንጂ አልቀነሰም። 
  
4.     በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በቅዱስ ሲኖዶሱ የተወሰኑት ውሳኔዎችንም ለማስፈፀም አለመቻሉ በቤተ ክርስቲያቱ ውስጥ ነው በዝርፊያና የቤተ ክርስቲያን ሰላም በማደፍረስ ምዕመኑን ተፋ በማስቆረጥ ራ ላይ የተሰማሩት ቡድኖች ቤተ ክርስቲያኒቱ ብሎም በሀገሪ ሰላም እና ልማት ላይ ከፍተኛ አደጋ እንደሚጥሉ ማወቅ ማስረጃና ጥልቅ ምርምር አያሻውም።
5.     አሁንም ቢሆን መንግሥት በራሱ የሚያደርገውን አስተዳደራዊ በደል ምዕመኑ የሚታገሰውን ያህል በእምነቱ ሲመጣበት ሊታገስ እንደማይችልና የቤተ ክርስቲያ ዶግማና ቀኖና እንዲጠበቅ፤ ብቷ እና ንብረቷ እንዳይዘረፍ፤ እንዲሁም የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረድ እንዲጠበቅ አስፈላጊውን መስዋዕትነት መክፈል እንደሚችል አውቆ መንግሥትያስብበት ይገባል

6.     በፖለካው ረገድ በቅርቡ በሰሜን አፍካ በኢ-ፍትሐዊ አስተዳደሮች ላይ የተደረገው ዓይነት ሕዝባዊ አመ ለመሪዎች መባረ ምክንያት እንደሆነው ሁሉ ይህ በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚደረገው በደል ማቆም ካልተቻለ በኢትዮጵያ ምዕመ ወደዚህ ዓይነት ቁጣ ሊራመድ እንደሚችል መንግሥት ሊረዳው ይገባል።

7.     ስለሆነም የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረድ እንዲጠበቅ እና በቤተ ክርስቲያንቱ የበላይ ጠባቂና ወሳኝ አካል በሆነው በቅዱስ ሲኖዶስ እና በየደረጃው ባሉ እውነተኛ የቤተ ክርስቲያን አመራር አካላት የሚወሰኑት ውሳኔዎችና አመራሮች በእምነቱ ቀኖናዊ አራር መረት ተፈሚ እንዲሆኑና ከላይ ለተጠቀሱት ለእውነተኛ የቤተ ክርስቲያንቱ አካላት መንግሥት  አስፈላጊውን የግ ከለላሰጥ ይገባል እንላለን።

8.     መንግሥት የሀገሪቱን ሰላም ለማስከበር የቤተ ክርስቲያኗን ሰላም ማስከበር ይጠበቅበታል

ቸር ወሬ ያሰማን፣ አሜን


አጀንዳችን አንድ ነው - ሃይማኖታችን እና ቤተ ክርስቲያናችን ብቻ!!!!!!



(ደጀ ሰላም፤ ሜይ 13/ 2011)፦  ላለፉት ሦስት እና አራት ዓመታት በተደጋጋሚ ስናሳስብ እንደቆየነው ቤተ ክርስቲያናችንን ከፊት ከኋላ፣ ከግራ ከቀኝ እና ከውስጥ ጠፍንገው የያዟት ችግሮች የበለጠ እየተገለጡ፣ ፈተና የሆኑባት ግለሰቦችም የበለጠ እየታወቁ፣ በሕዝቡ ዘንድ ይፈጥሩ የነበሩትም ብዥታና ግርታ የበለጠ እየጠራ በመምጣት ላይ ይገኛል። ቤተ ክርስቲያን በውስጥም በውጪም ብዙ ፈተናዎች የተደቀኑባት ቢሆንም ከውስጥ ተቀምጠው፣ እንጀራዋን እየበሉ ተረካዛቸውን የሚያነሱባት ግን ፋታ የሚሰጧት አልሆኑም። እነዚህን የቤተ ክርስቲያን ፈተናዎች እና የተሰጣቸውን አደራ አራካሾች ሳናሰልስ ተግባራቸውን በመቃወምና ለምእመኑም ለማሳወቅ በመጣር ላይ እንገኛለን። እነዚህ የቤተ ክርስቲያን ፈተናዎች የተንጠለጠሉበት ካስማ ደግሞ ሁለት ነው። አንደኛው ሙስና፣ ሁለተኛው ኑፋቄ። ደጀ ሰላምም በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ የሰፈነውን ሙስና ትቃወማለች፣ ሰርገው የገቡትን መናፍቃን እና የሚዘሩትን ኑፋቄ ትጸየፋለች። ምን ማለታችን እንደሆነ እናብራራው።


በየትኛውም መንግሥታዊም ሆነ መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም ውስጥ ይብዛም ይነሥም ሙስና መኖሩ ይታወቃል። በአገራችን ደረጃ ከተመለከትነው በየደራጀው ሙስና እንዳለ በዚህም ምክንያት ከሥልጣናቸው የተባረሩ ሰዎች መኖራቸውን በመገናኛ ብዙሃን እንሰማለን፣ እንመለከታለን፣ እናነባለን። የሙስናው አየር ከነፈሰባቸው ተቋማት መካከል ደግሞ ግንባር ቀደምነቱን ሊይዝ የሚገባው የቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደር ነው። ስለዚህ ጉዳይ በተደጋጋሚ የጻፍን በመሆኑ አንመለስበትም። በጠቅላላ ለማስቀመጥ ግን ያለ አግባብ በሥልጣን በመባለግ፣ እጅ መንሻ ወይም ጉቦ በመቀበል፣ ከምእመናን የተሰበሰውን ገንዘብ እና ቁሳቁስ ለግል ጥቅም በማዋል፣ የትኛውንም ጉዳይ ለማስፈጸምም ሆነ ተመሳሳይ ተግባር ለማከናወን ጉቦን እንደ መፍትሔ መጠቀም እጅግ በጣም ሰልጥኗል። ይህ ብልሹ አሠራር በጊዜው እንዳይገታ ደግሞ የቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደር ፍላጎትም ችሎታም የለውም።

ሙስና በምድራዊ ሕግ ብቻ ሳይሆን በመንፈሳዊውም ሕግ የተጠላ እና የተከለከለ ቢሆንም ሃይማኖታዊውን ሕግ የሚያውቁ እና የመንፈስ ልዕልና ኖሯቸው ሌላውን በትምህርታቸው ተግሳጽ፣ በቃላቸው ምክር ሊያቀኑ የሚገባቸው ሰዎች እና ይህንን ልታደርግ ይገባት የነበረች ተቋም የዚህ መፈብረኪያ ስትሆን በሽታው መድሃኒት ሊያገኝ አይችልም። የበሽታ ማጥፊያ መድሃኒቶችን እንደሚላመዱ የበሽታ አምጪ ሕዋሶች፣ ቃለ እግዚአብሔር እና ኢትዮጵያዊ ሥነ ምግባርን በመጣስና በመደምሰስ ዓይን ያወጣ ዝርፊያ በማጧጧፍ ላይ ናቸው።

ሠራተኛ መበደል፣ ንብረት ማባከን፣ ጉቦ መቀበል በዚህም ደግሞ የራስን ንብረት ማከማቸት ለካህን እና ለክህነት የማይገባ ድርጊት መፈጸም የአደባባይ ምሥጢር ሆኗል። ይህም ከርዕሰ ቤተ ክርስቲያኑ ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጀምሮ የሚታወቅ ቢሆንም እርሳቸውም የችግሩ አካል በመሆን ቤተ ክርስቲያኒቱን ወደ ውድቀት አፋፍ ከመግፋት ውጪ ራሳቸውም ድርጊቱን ተጸይፈው ሌላውን ሊወቅሱ አልቻሉም። በዙሪያቸው በሰበሰቡት የቤተ ዘመድ ጉባኤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሲያስነቅፉ እና ሲያዋርዱ ዓመታት አስቆጥረዋል። አሁንም ቀጥለዋል።

ይህም ሳያንስ አሁን ደግሞ ቤተ ክርስቲያኒቱን በተሐድሶ የኑፋቄ ትምህርት ለማበላሸት ለሚፈልጉ ሰዎች ነገሮችን በማመቻቸት ችግሩን የበለጠ አስፈሪና አስቸጋሪ አድርገውታል። ገንዘብ ቢዘረፍ በገዘንዘብ ይተካል። ንብረት ቢወድም በንብረት ይካካሳል። እምነት ከተበላሸ ግን በምን ይስተካከላል?

ኢትዮጵያ ሕብረ-እምነት ያላት አገር መሆኗን እናምናለን። ኢትዮጵያ የአንድ እምነት ብቻ የሚል ጅል አስተሳሰብ የለንም። ሁሉም የየራሱን እምነት አክብሮ እስከኖረ ድረስ አንድ ሰው ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት የተለየ አስተሳሰብ ስላራመደ ችግር ይገጥመው ዘንድ አንመኝም።፡ ለዚህም ነው ጥቂት አክራሪ ሙስሊሞች በጅማ አካባቢ በፕሮቴስታንቶች ላይ ያደረሱትን አደጋ አምርረን የተቃወምነው። ነገ በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ ተመሳሳይ ችግር ቢደቀን አብረናቸው ከመቃወም ወደ ኋላ አንልም። ነገር ግን የሌላ እምነት፣ ቡድን እና ግለሰብ በእምነት መፈጸሚያ ቦታችን እና በመዋቅራችን በድብቅ ሰርጎ በመግባት የሚፈጽመውን ተንኮል አጥብቀን እንቃወማለን። ተሐድሷውያን ፍፁም የለየላቸው ፕሮቴስታንቶች ሆነው ሳለ በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ የሚፈጽሙትን ደባ አምርረን የምንቃወመው ያለ እምነታቸው እና ያለ ቤታቸው በመግባታቸው ነው። ጦማሪው ዳንኤል ክብረት በአንድ ጽሑፉ እንዳለው “ሤራ፣ ተንኮል፣ ስለላ፣ ማጭበርበር እና እምነት ምን አገናኛቸው?” በቤታችንስ ማን አስገባቸው? እስካልወጡ ድረስም እንቅልፍ አይኖረንም እንላቸዋለን። ይህ ደግሞ የደጀ ሰላም ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኦርቶዶክሳውያን አቋም እና እምነት ነው።

ቤተ ክርስቲያናችንን ፈተና የሆኗት እነዚህ ሁለት ቡድኖች (ሙሰኞች እና ተሐድሶዎች) ዓላማቸውን ለማስፈጸም የጋራ ግንባር በመፍጠር እንደሚሠሩ ከዕለት ዕለት ግልጽ እየሆነ መጥቷል። ግልጽ ሆነ ያልነው ለእኛ ሳይሆን የችግሩን መኖር ይጠራጠሩ ለነበሩ አካላት ነው። ሙሰኞቹ ገንዘብ እስካገኙ ድረስ ቤተ ክርስቲያኒቱን ከመሸጥ አይመለሱም። ተሐድሶዎቹ ደግሞ ዓላማቸውን የሚያስፈጽምላቸው ሰው እስካገኙ ድረስ ገንዘብ ለመስጠት እና ለመተባበር ወደኋላ አይሉም። ለዚህም ነው ትናንት የተጣሉ ይመስሉን የነበሩ ሰዎች ዛሬ ግን እጅግ የሚዋደዱ መስለው በሕብረት ቆመው የምናያቸው። እነዚህ ሁለት ቡድኖች ደግሞ ዓላማቸውን የሚያሰናክልባቸው የመሰላቸውን ማንኛውንም አካል ከማጥፋት ወደኋላ አይሉም። አላሉምም። ሁለቱም ወገኖች ዓላማቸውን ለማስፈጸሚያነት፣ የሚቃወማቸውን ለማጥቂያነት ለመጠቀም የሚፈልጉት መንግሥትን እና ያለውን አስተዳደራዊ መዋቅሩን ነው። መንግሥት ለእነዚህ ወገኖች በመጠቀሚያነት ይውላል የሚል እምነት ባይኖረንም ሙከራቸው ግን እንዳለ እርግጠኞች ነን። ይህ ደግሞ ጥንትም የነበረ እንጂ አዲስ የመጣ ዘዴ አይደለም።

ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚያስተምረን አይሁድ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ከከሰሱባቸው ክሶች መካከል አንደኛው ከሮማውያን ገዢዎቻቸው ጋር ለማጋጨት የተጠቀሙበት “ራሱን የአይሁድ ንጉሥ  ነኝ ይላል” የሚለው ፖለቲካዊ ክስ ነው። ንጉሥ በንጉስነቱ፣ ወንድ ልጅ በሚስቱ፣ እግዚአብሔር በመለኮቱ ሲመጡበት … እንደሚባለው ጌታን ከሮም ቤተ መንግሥት ጋር በማጋጨት ሊያሰቅሉት ሞክረዋል። ይህ በጌታችን ላይ የተደረገው ነገር በየዘመኑ በተለያየ መልክና ቅርጽ ሲፈጸም ኖሯል።

ሌላውን ትተን በተለያየ ዘመን በአገራችን እንኳን የነበረውን ሁኔታ ብንመለከት እበላ ባይ ደባትር በነገረ ሰሪነት ወደ ነገሥታቱ በመቅረብ ንፁሐን እና ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ሰዎች ላይ አደጋ ሲያደርሱ ኖረዋል። “እገሌ እና እገሌ በሥልጣንህ መጥተውብሃል” በሚለው ክፉ ወሬያቸው የብዙዎችን ደም አስፈስሰዋል። ብዙዎችንም በግዞት እንዲጣሉ፣ በእግር ብረት እንዲታሰሩ፣ በብቸኝነት እንዲንከራተቱ፣ አገር ጥለው እንዲሰደዱ አስደርገዋል። ለአብነት የደብረ ሊባኖሱን ቅዱሱን የአባ ፊሊጶስን ግዞት እና ግርፋት፣ የጋስጫውን የአባ ጊዮርጊስን ግዞት፣ የነአባ በጸሎተ ሚካኤልን መከራ መጥቀስ ይቻላል።

እነዚህ ነገሥታት በቅዱሳኑ ላይ መከራ ያጸኑባቸው በነገረ ሠሪዎቹ ተታለው እንጂ ራሳቸው ክፉዎች ነገሥታት ስለነበሩ አልነበረም። በሌሎች መልካም ተግባሮቻቸው የተመሰገኑ መሆናቸውን ታሪክ ይነግረናል። ይሁን እንጂ ቤተ ክህነቱን መጠጊያ የሚያደርጉ ተንኮለኞች በሚፈጽሟቸው በደሎች ብዙዎች የመከራው ቀንበር ይወድቅባቸዋል። በዚህ ዘመንም የኢሕአዴግ አባላት ነን፣ በመንግሥት ዘንድ ሞገስ አለን፣ ሥልጣን አለን፣ የአገር ልጅነት እና አምቻ ጋብቻ አለን የሚሉ ሰዎች ብዙ መልካም ሰዎች ላይ የመከራ ቀንበር በማስጫን ላይ ናቸው።

እነዚህ በክህነታቸው በቤተ ክህነት፣ በፓርቲ አባልነታቸው ከመንግሥት የተጠጉ ጥቅመኞች ቤተ ክርስቲያኒቱን እየጎዱ ነው፤ የመንግሥትንም ስም እያስጠፉ ነው። ራሳቸውን የመንግሥት  ብቸኛ ወገንና ልጅ፣ ሌላውን ባዳና የእንጀራ ልጅ አድርገው በማቅረብ በአንድ አገር ሁለት ዜጋ ያለ እያስመሰሉ ነው። የመንግሥት መንግሥትነቱ ለእነርሱ ብቻ ሳይሆን ለእኛም ነው። በሕግ ፊት ሁላችንም እኩል ነን። ይሁን እንጂ እነዚህ ሰዎች በሚፈጽሙት ወንጀል ተያቂ ባለመሆናቸው በብዙው ምእመን ዘንድ ከሕግ በላይ የሆኑ አስመስሏቸዋል።

በአገራችን ልማት እንዲመጣ እንመኛለን። አመጽን፣ ብጥብጥን፣ በእምነቶች መካከል ሊከሰት የሚችልን አለመቻቻል እንቃወማለን። ይህም ብቻ ሳይሆን በቤተ ክርስቲያናችን ያለውን ሙስና እና ሰርጎ የገባ ተሐድሷዊ የመናፍቃን ተንኮልም እንቃወማለን። እነዚህን ሙሰኞች እና ተሐድሶዎች የምንቃወማቸው ባላቸው የፖለቲካ አቋም ሳይሆን በእምነታችን ላይ በሚፈጽሙት ወንጀል ነው። አጀንዳችን አንድ እና አንድ ነው፦ እነዚህን የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች መቃወም።