Friday 3 January 2014

እነሆ የጌታ ልደት ደረሰ

ከታምራት ፍሰሃ
ፌስቡክ ገጽ ላይ የተወሰደ

እነሆ የጌታ ልደት ደረሰ ፡ የጭፈራ ጊዜም ደረሰ ፡ የዳንስና የእስክስታ የመጠጥና የዝሙት ጊዜም ደረሰ። ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን የጌታዋን ልደት ድምጿን ከፍ አድርጋ ታውጃለች ፤ የዚህ አለም ገዢ ዲያቢሎስ ደግሞ ይህን ቅዱስ ጥሪ ማንም እንዳይሰማው ይህን አለም በልዩ ጩኸት በክሎታል ፤ ጭኸቱንም በሚዲያዎች በኩል ያደርጋል። “እንኳን ለጌታ ልደት አደረሳችሁ” ይሉናል። ቀጠል አድርገውም “እዚህ ክለብ ብትሄዱ ለገና ልዩ ዝግጅት ተዘጋጅቷል ፡ ጭፈራው ዘፈኑ ሌላ ነው ፡ መጠጡ ምግቡ ልዩ ነው ፡ ሆይታው ሞቅታው ልዩ ነው ፡ ኑ ና ጌታችሁን እያሳዘናችሁ የዲያቢሎስን ፈቃድ ፈፅሙ” ሲሉ በጥበብ እንሰማቸዋለን፤ በጌታችን ልደት ሰይጣን የሚከብርበት ፡ በክርስቲያኖች ልደት ዲያቢሎስ የሚደምቅበት ፡ በመድሃኒት ክርስቶስ መገለጥ ፡ የዚህ አለም ገዢ ሃሳዊው መሲህ የሚታይበት ይህ ዘመን እንደምን ክፉ ነው?

ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ በማህበረ ቅዱሳን


ሰበር-ዜና ውስጠ ተሃድሶ የሆኑ ጥቂት ሰባክያን አንገታቸውን ቀና ቀና ማድረግ ጀመሩ

 ሱላማጢስ
በቅርቡ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተጀመረውን ሥር ነቀል አስተዳደራዊ ለውጥ ተከትሎ ብቅ ብቅ ያሉ ውስጣቸው ተሃድሶ የሆኑ ጥቂት ሰባክያንና የአድባራት አስተዳዳሪዎች በቤተ ክርስቲያኒቱ የተስፋፋውን የኑፋቄና የሙስናን በሽታ ከሥሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነቅሎ ለመጣል በሚደረገው ከፍተኛ እንቅስቃሴ የተነሳ ይኸው በሽታ የተቆራኛቸው እነ መላከ መንክራት ኃይሌ አብርሃ፣ አባ ሠረቀ እና ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ፣ ሊቀ ትጉሃን ዘካርስ፣ መላከ ብስራት መላክ አበባውን ጨምሮ በሙስናና በኑፋቄ የተጨማለቁ ግለሰቦች ለለውጡ እንቅፋት ለመሆን ዋና ተዋናዮች ናቸው፡፡