Tuesday 24 December 2013

ቤተ ክርስቲያን ከ290 ሚልዮን ብር በላይ በኾነ ውጭ ሁለገብ የሥልጠና ማዕከል ልትገነባ ነው




የአደረጃጀትና አሠራር ጥናት ሰነዱ አካል የኾነው የሥልጠናና የሰው ሀብት ልማት ፖሊሲው ከአፈጻጸም ዝርዝር መመሪያው ጋራ ተዘጋጅቷል የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናታዊ ውይይቱ ተጠናቅቋል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን÷ ከአድልዎና ሙስና የጸዳ፣ ሥርዐተ እምነትዋን የሚጠብቅ፣ መንፈሳዊ ዕሴቶችዋን የሚያንጸባርቅ፣ ሞያዊ ብቃትን ማዕከል ያደረገ፣ ዘመኑን የዋጀና የተቀላጠፈ አሠራር እንዲኖራት ያስችላል የተባለ ሁለገብ የማሠልጠኛ ማዕከል ለመገንባት የፕሮጀክት ጥናቱን አጠናቅቃ ማዘጋጀቷ ተገለጸ፡፡