Sunday 2 September 2012

በዚህ ወቅት የቤተክርስቲያን አበውም ሆነ ምዕመናን ለረሷቸው የዋልድባ መነኮሳት ትሁን ይህቺ ዜማ 



የፓትርያርኩ ቀብር ላይ ትልቁ ስህተት


(አንድ አድርገን ነሐሴ 27 2004 ዓ.ም)፡-ፓትርያርኩ ቅዳሴውን አቋርጠው ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህዳሴውን አቋርጠው ከዚህኛ ዓለም ወደዚያኛው ዓለም ከሄዱ ቀናት ተቆጥረዋል ፤ ቤተመንግሰቱም ሆነ ቤተክህነቱ አስጨናቂ የሆነ የሀዘን ድባብ ወርሶታል ፤ የፓትርያርኩ አስከሬን ለ6 ቀናት አፈር ሳይቀምስ ሲቆይ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ደግሞ ለ13 ቀናት ያህል ቆይቷል ፤ የፓትርያርኩን ሥርዓተ ፍትሐት ላይ የምስራቅ አብያተ ክርስትያናት ፤ የግብጽ ኦርቶዶክስ ፤ የአርመንና የህንድ ኦርቶዶክስም ጸሎተ ፍትሀት አድርገዋል ፤ ከእነዚህ አብያተክርስትያናት ጋር የኢትዮጵያ ኦርዶክስ ተዋህዶ እምነት የዶግማና የእመነት አንድነት ስላላት  ጸሎተ ፍትሀት ማድረጋቸው በስርዓተ ቤተክርስትያናችን ተቀባይነት አለው፡፡ 


በዋልድባ የመነኰሳቱ ስደት፣ እስርና ድብደባ ተባብሶ ቀጥሏል

·         የተሰደዱት መነኰሳትና መናንያን ቁጥር 13 ደርሷል::
·         ሁለት መነኰሳት በማይ ገባ ወረዳ ታስረዋል::
·         በጠ/ሚኒስትሩና በፓትርያርኩ አሟሟት “ውዥንብር ፈጥራችኋል” በሚል ተከሰዋል::
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 27/2004 ዓ.ም፤ September 2/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦  በቤተ መንግሥቱም በቤተ ክህነቱም በተመሳሳይ ወቅት የደረሰብን ሐዘን አነጋጋሪ ከመኾን አልፎ ፍትሐ እግዚአብሔር የተፈጸመበት፣ የእግዚአብሔር መልእክትም የተላለፈበት እንደ ኾነ እየተነገረ ነው፡፡ እንደ አቶ ስየ ኣብርሃ ያሉ የተቃውሞ ፖለቲካ መሪዎች ሳይቀሩ በኹኔታው ላይ ቆም ብለን እንድናስብ እየመከሩ ናቸው፡፡