Tuesday 9 October 2012

ዋልድባን ለመታደግ በዋሽንግተን ዲሲ ትላንት ጉባኤ ተደረገ፣ ይበል የሚያሰኙ እንቅስቃሴዎችም ተደርገዋል






በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ 

በትላንትናው ዕለት መስከረም ፳፯ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ክርስቲያኖች አንድነት (ዋልድባን ለመታደግ የሚንቀሳቀሰው ዓለም አቀፍ ኮሚቴ ዋሽንግተን ዲሲ ንዑስ ክፍል) አስተባባሪነት የተጠራው ጉባኤ ተካሂዶ ውሏል። በጉባኤውም ላይ ካህናት አባቶች፣ ሰባኬ ወንጌል፣ እንዲሁም በርካታ ከዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው በመጡ የጉባኤው ታዳሚዎች በተገኙበት በርካታ ቁም ነገሮችን ተነጋግሮ እና ጉባኤው ተጠቃሏል። በቀጣይነትም ሥራዎችን በእቅድ ይዞ ለመሥራት ብሎም በአባባቢው የሚገኙትንም መዕመናን እንዲሁም በመላው ዓለም የሚገኙትን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አማኞችን በማስተባበር ለሥራ የተነሳሱ ካህናትን፣ መምህራንን፣ ዘማሪያን፣ በትውልድ ኢትዮጵያውያን የሆኑ በምዕራቡ አለም በተለያየ ሀላፊነት ላይ ያሉትን ምሁራንን እንዲሁም አጠቃላይ የኢት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምዕመናን በማስተባበር የዋልድባ ገዳም መፍረስ ሳይሆን አፈሯ እንኳን እንዳትነካ (ሳትነካ) ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ ቁርጠኝነት ያሳዩበት እና በብዙ ሃዘንም እየደረሰ ያለውን እንግልት በተለያየ መልኩ ለማሳየት ተሞክሯል።