Sunday 18 May 2014

ዜና ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ: መዝሙር አለቀሰ

ዜና ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ: መዝሙር አለቀሰ

መዝሙር አለቀሰ

መዝሙር አለቀሰ
የያሬድ ዝማሬ፣ የአዘማመር ስልቱ
የበገናው ቃና፣ማሲንቆ ቅኝቱ
የከበሮው ውበት የዋሽንት ፍሰቱ፡


ነበር ተፈጥሯቸው ስብሐት ሊዘሩ
ሥርዓት ሊያከብሩ
መንፈስን አድሰው ውበት ሊደምሩ
ምህላ ሊያደርሱ ኑዛዜ ሊያወሩ
ስንዱዋ እመቤት ቤተ ክርስቲያን ቅድስት
እንዳላስተማረች ሁሉን በሥርዓት


ዛሬማ አፍ የፈታ ሁሉ እያንጎራጎረ፣
ቀኖና ትውፊቱን እየሸረሸረ
የመዝሙር ሥርዓቱ ስልቱ ተቀየረ
መዝሙር ዜማ ሳይሆን ጩኸት ሆኖ ቀረ
ለነፍስ ሐሴት ትቶ ለሥጋ አደረ


ሳኦልም ከደዌው እንዳልተፈወሰ
ወኅኒውም በመዝሙር እንዳልፈራረሰ
መዝሙር ቅዱሳንን እንዳላወደሰ
ዜማን ሐዘን ገባው መዝሙር አለቀሰ


ንጉሥ ገብረ መስቀል ጦር ከእግር ሰክቶ
በፍጹም ተመስጦ አለምን ረስቶ
እንዳልነበር ሁሉ ጸጋችን ምግባችን
መዝሙር አንገት ደፋ ከመላእክት በላይ አዋቂዎች ሆነን


ሳይጠፋ መዝሙሩ እስከ ሥርዓቱ
ፈር እየለቀቀ ዘማሪ ነኝ አለ ሁሉም በየቤቱ
በጠፋበት ሁሉ ተሰጥኦው መክሊቱ
መዝሙር አለቀሰ ተገፍቶ መብቱ
ተጥሶ ሥርዓቱ።
ምንጭ
ገድለ ቅዱሳን Gedle Kidusan Acts of Kidusan

Friday 16 May 2014

ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተ ክርስቲያን

መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ

ብዙዎች ኢየሱስ ክርስቶስን ቤተ ክርስቲያን እንደማትሰብክ አድርገው ለማቅረብ ይሞክራሉ፤ ነገር ግን ሐዋርያዊት የኾነችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ስለክርስቶስ ያላስተማረችበት ጊዜ የለምም አይኖርም፤ ደግሞም እናት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በጊዜያችን አንዳንዶች መናፍቃን የኢየሱስን ክብር አሳንሰው ከአብ በታች አድርገው እንደሚያስተምሩት ሳይኾን በእውነት ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክብሩ የተካከለ፣ ቅድመ ዓለም የነበረ አኹንም ያለና ዓለምን አሳልፎ የሚኖር፤ ለፍርድ ዳግመኛ የሚመጣ፤ እውነተኛ ፈራጅ የአማልክት አምላክ የነገሥታት ንጉሥ ነው ብላ የምታስተምረው፡፡ ይኽ ብቻ ሳይኾን ሥጋውን ደሙን በምትሠዋበት በቃል ኪዳን ታቦቱም ላይ “ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው” (የሕያው የአብ የባሕርይ ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ) ብላ አክብራ ስሙን ትጽፋለች እንጂ በድፍረት ሆና ስሙን መቀለጃ አታደርግም፡፡