Friday 14 December 2012

ደም መስጠት እና የሰውነት አካልን መለገስ ይፈቀዳል?

በዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ
ከፌስቡክ ገጽ ላይ የተወሰደ

የሰው ልጅ በዚህች የመከራ ቦታ በሆነች ምድር እስካለ ድረስ ብዙ ፈተናዎች ያጋጥሙታል፡፡ ከሰው ልጅ ውድቀት በኋላ ‹‹ራስ ሁሉ ለሕመም ልብም ሁሉ ለድካም ሆኗል ፤ ከእግር ጫማ አንሥቶ እስከ ራስ ድረስ ጤና የለውም›› ኢሳ. 1.5
ከሚቻለን በቀር እንድንፈተን የማይፈቅደው እግዚአብሔር ‹‹ከፈተናው ጋር አብሮ መውጫውን ያደርግላችኋል፡፡›› ተብሎ እንደተነገረ የሰው ልጅ በተሰጠው ብሩሕ አእምሮ ተጠቅሞ በሚያድንበት የሕክምና ጥበብ እንዲራቀቅ አድርጓል፡፡ እኛ ክርስቲያኖችም ሐኪሙ የአርብ ዕለት ፣ የሚሰጠው መድኃኒት ደግሞ የማክሰኞ ዕለት ፍጥረታት መሆናቸውን በማሰብ የሰው ልጅ ስለደረሰበት የህክምና ጥበብ እግዚአብሔርን እናመሰግናለን፡፡ ማዳን የእርሱ ነውና ፤ ሐኪሞቹ ሌላ ፣ ህክምናው ሌላ ቢሆንም ፈዋሹ እርሱ እግዚአብሔር መሆኑን እናምናለን፡፡