Monday 9 December 2013

በፔርሙዝ ተለውጦ አሜሪካ የተሻገረው የ400 ዓመቱ ብራና


08 December 2013 
ተጻፈ በ ፍቅር ለይኩን
(ከአንድ አድርገን ድረ-ገጽ ላይ የተወሰደ)

የቅርሶቻችን ዋጋ ምን ያህል ነው?

(ሪፖርተር ጋዜጣ):- የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ)...በዓለም ጥንታዊ ቅርስነትከመዘገባቸው የሥነ ጽሑፍ ውጤቶች መካከል በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ባለቤትነት የተመዘገቡና በብራና ላይ የተጻፉ የመጽሐፍቅዱስ ክፍሎች የነገረ ሃይማኖት ጽሑፎች ይገኙበታል፡፡

እነዚህ እስከ ሺሕ ዓመታት ዕድሜን ያስቆጠሩ ብርቅና ውድ የሆኑየሥነ ጽሑፍ ቅርሶች በተለያዩ ጊዜያት በአገሪቱ በደረሱ ተፈጥሮአዊናሰው ሠራሽ አደጋዎች ምክንያት ውድመት፣ ጥፋትና ዝርፊያእንዳጋጠማቸው ይታወቃል፡፡ከዚህም በተጨማሪ በጥናትና በምርምር ሰበብ ከአገር የወጡ ጥንታዊ ብራናዎች አያሌ ናቸው፡፡በአውሮፓና በአሜሪካ በሚገኙ ትላልቅ ዩኒቨርሲቲዎችና አብያተ መጻሕፍት፣ እንዲሁም በግለሰቦች፣ በቅርስ አሻሻጮች እጅም ማግኘትየተለመደ ነው፡፡