Monday 3 September 2012

ፓትርያርክ ጳውሎስና ያስፈጇቸው ሊቃነ ጳጳሳት

an article about Abune paulos EGYPT ETHIOPIA AFRICAN UNION SIDELINES
ገብረ ኪዳን

የፓትርያርክ ጳውሎስን ሞት ተከትሎ ፣ ታዋቂው ደራሲና ሰባኪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት “ለምጣዱ ሲባል አይጧን ” በሚል ርእስ ፣ አጭር ግን ጠንካራ መልእክት ለመላው ኢትዮጵያውያን አስተላልፎ ነበር ።


የጽሁፉም ዋና ጭብጥ አንድና ግልጽ ነው— ለቤተ ክርስትያኒቱ ክብር ሲባል ለተወሰኑ ቀናት ስለፓትርያርኩ ክፉ ስራና ደካማ ጎኖች የሚያትቱ ጽሁፎችምሆነ ውይይቶች አንዲዘገዩ “ የሚማጸን ነበር ። ለቤተ ክርስትያኗ ክብር ሲባል መራሄ ቤተ ክህነቱ አቡነ ጳውሎስ ከበቂ በላይ የሀዘን ( ይገባቸዋል ብዬ ባላምንም) ስርአት ተካሂዷል ። እነሆ አሁን በዘመናቸው ስለተከናወኑ አሰቃቂና አስጸያፊ ወንጀሎች እናውሳ።

ሟች ፓትርያርክ ጳውሎስ ይወቀሱበትና ይከሰሱበት የነበሩት ወንጀሎች ብዙ ናቸው። በሃይማኖት ጉዳይ አለቃ አያሌው በመፍቀሬ ካቶሊክነት ሲወቅሷቸው ፣ አቡነ አብርሃምና ሌሎች በርካታ ኦርቶዶክሳውያን ሊቃነ ጳጳሳት ደግሞ ጥንተ አብሶን በተመለከተ ፓትርያርኩ በመመረቂያ ጽሁፋቸው ላይ በጻፉት ኢ – ኦርቶዶሳዊ ትምህርት አንቀው ይዘዋቸው ነበር። በገንዘብ አባካኝነትና በሙስና ሲወቀሱ የነበሩት ፓትርያርክ ጳውሎስ ፣ ህይወታቸው ሲያልፍ በዘመዶቻቸው አካውንት አስከፍተው ያስቀመጡት 22 ሚሊዮን ብር መገኘቱ በሙስና የሚቀርብባቸውን ወቀሳ እውነተኛነት ያመላክታል። ሌሎችም ብዙ መረጃና ማስረጃ የተገኘባቸው ክፉ ስራ ቢኖራቸውም እኔ ግን የትኩረት ነጥቤ የሳቸውን ስልጣን ከመጠበቅ ጋር በተያያዘ በምስጢር የተገደሉትን የሊቃነ ጳጳሳትና የሊቃውንተ ቤተ ክርስትያን ህይወት ይመለከታል።

ስንክሳርንና ግብረ ሕማማትን ወደ አማርኛ የተረጎሙት ሊቅ ዐረፉ


(MKWebsiteነሐሴ 28/2004 ዓ.ም/ August 3/2012/ በእንዳለ ደምስስ/ PDF):- ስንክሳርንና ግብረ ሕማማትን እንዲሁም ሌሎችን መጻሕፍት ከግእዝ ወደ አማርኛ የተረጎሙት ታላቁ የመጻሕፍት ሊቅ ሊቀ መዘምራን ላእከ ማርያም ወልደ ኢየሱስ በተወለዱ በ90 ዓመታቸው ነሐሴ 1 ቀን 2004 ዓ.ም. በሞተ ስጋ ከዚህ ዓለም ተለዩ፡፡ ሊቀ መዘምራን ላእከ ማርያም ወልደ ኢየሱስ በአርሲ ክፍለ ሀገር በጢዮ ወረዳ ልዩ ስሙ ጨቢ አቦ በተባለ አካባቢ ከአባታቸው መምህር ወልደ ኢየሱስ ዘነበ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ወለተ ሩፋኤል ብስራት ነሐሴ 16 ቀን 1915 ዓ. ም. ተወለዱ፡፡

ከአባታቸው ከመምህር ወልደ ኢየሱስ ዘነበ ንባብ፤ ውዳሴ ማርያም ንባብና ዜማ ፤መዝሙረ ዳዊትና ግብረ ዲቁና በመማር ለስልጣነ ክህነት ከበቁ በኋላ በአካባቢያቸው በሚገኘው ዱግዳ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በዲቁና ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡

ደቂቀ ናቡቴ Dekike Nabute: ኑዛዜ

ደቂቀ ናቡቴ Dekike Nabute: ኑዛዜ: በዲ/ን ሕብረት የሽጥላ ራ ስን ለካህን ማሳየት ይገባል:: ኃጢአትን ለካህን መናገር አይገባም ለሚሉ ::  ይህንን ልናስደምጣችሁ የፈለግንው መናፍቃን እና ፕሮቴስታንት ተሓድሶዎች ኃጢአትን  ለካህን መና...