Saturday 21 July 2012

በዋልድባ መነኰሳት ላይ የሚካሄደው እስርና እንግልት ተባብሶ ቀጥሏል


  • አንድ የዋልድባ አብረንታንት ገዳም መነኰስ ወደ ማይ ፀብሪ ተወስደዋል።
  • የገዳሙ መነኰሳት የግዴታ መታወቂያ እንዲወስዱ ተደርገዋል።
  • ፓትርያርኩ ዕግድ የጣሉበት የጀርመን የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሒዷል።
(ደጀ ሰላም፤ ሐምሌ 14/2004 ዓ.ም፤ ጁላይ 21/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦ የወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት በዋልድባ ገዳም ህልውናና ክብር ላይ በሚያደርሰው ተጨባጭ አደጋና ታሳቢ ስጋቶች የተነሣ የፕሮጀክቱን አተገባበር በሚቃወሙ የዋልድባ ማኅበረ መነኰሳት ላይ የሚደርሰው እስር፣ እንግልትና ድብደባ ተባብሶ መቀጠሉን የሥፍራው ምንጮቸ ለደጀ ሰላም ገልጸዋል፡፡ በተለይም የፀለምት - ማይ ፀብሪ ወረዳ አስተዳደር በየጊዜው በመነኰሳቱ ላይ በሚወስደው የግፍ ርምጃ በሠቆቃ ውስጥ የሚገኙት ማኅበረ መነኰሳቱ ከሰኔ 21 - ኅዳር 8 ቀን የሚዘልቀው የገዳሙ የሱባኤ ወቅት እንደታወከ ተዘግቧል፡፡


የህይወትን መዝገብ ቃሉን ያስነበቡህ
የተዋህዶ አርበኞች ቅዱሳን ዋኖችህ
የድካም ዋጋቸው የእምነታቸው ፍሬ 
ያማረ ነውና ምሰላቸው ዛሬ