Tuesday 21 August 2012

የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የፓትርያርክ አመራረጥ ተሞክሮ How Do We Elect A New Pope? - Your Voice TV


ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ኾነው ተመረጡ

  • ቋሚ ሲኖዶሱን የሚያጠናክሩ ብፁዓን አባቶች ተመርጠዋል::
  • ሕገ ቤተ ክርስቲያን ስለ ዐቃቤ መንበረ ፓትርያር ምን ይላል? (ከዜናው መጨረሻ ላይ ያንብቡት
    )
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 14/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 20/ 2012/ PDF)፦ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዛሬ፣ ነሐሴ 14 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀትር በፊት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ አድርጎ መርጧል፡፡ ስለዚህም ጉዳይ ዛሬ በ9፡00ሰዓት በቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡

ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ለመሠየም ምልአተ ጉባኤው ባካሄደው ምርጫ ሦስት ዕጩዎች ቀርበው እንደነበር የጉባኤው ምንጮች ለደጀ ሰላምተናግረዋል፡፡ በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 17 መሠረት ለምርጫ የቀረቡትና በሹመት ቀደምትነት ያላቸው ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት÷ ብፁዕ አቡነ ማቲያስ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሰሜን ጎንደር ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው፡፡


ቅ/ሲኖዶስ የቀብር ቀን እንዲቀየር የቀረበውን ጥያቄ አልተቀበለውም

  • የፓትርያርኩ ቤተሰቦች “በሕግ እንጠይቃለን” እያሉ ነው፤ ፓትርያርኩ የቤተሰቦቻቸው ወይስ የቤተ ክርስቲያን?
  • የሰላም እና አንድነት ጉባኤ ልኡካን አዲስ አበባ ይገባሉ፤ ጉባኤው ልዩነት በአንድነት ሳይፈታ ሌላ ፓትርያርክ የመሾሙን ጉዳይ ቅ/ሲኖዶስ እንዲያስብበት ተማፅኗል፤ የመንግሥትንም እገዛ ጠይቋል።
  • የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነትለፓትርያርኩ ሥርዐተ ቀብር አፈጻጸም ዝግጅት እያደረገ ነው።
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 15/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 21/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዜና ዕረፍት ከተሰማበት ቀን አንሥቶ አጠያያቂ ከኾኑት ጉዳዮች መካከል ሐዘናቸውን በሚገልጹ አንዳንድ ወገኖችና ብዙኀን መገናኛ ዘንድ የሚሰማው “ቤተሰቦቻቸው” የሚለው ቃል ነው፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሞት ተከትሎ የከሚሴ የጦር መሳሪያ ግምዣ ቤት በውሀቢያ ሙስሊም አክራሪዎች ተዘረፈ


·        "We are very glad about Meles' death. Ethiopia is sure to collapse,"Sheikh Ali Mohamud Rage, the spokesman for Al Shabaab told Reuters.

(አንድ አድርገን ነሐሴ 15 2004 ዓ.ም)፡- ቀናት አልፈው ቀናት ሲተኩ የሚሰማው እና የሚታየው ነገር ማህበረሰቡን እያስገረመው መጥቷል ፤ አዲስ ቀን በመጣ ቁጥር አዲስ ነገር ጠባቂ ጆሮዎች ተበራክተዋል ፤  አሁን የሰማው ግን አስደንጋጭ  ነው ፤ ሀገሪቱ በአሁኑ ሰዓት መተንፈስ እስኪሳናት ድረስ ውጥረት ውስጥ ገብታለች ፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት ፤ የፓትርያርኩ ዜና እረፍት እና ቀጣይ ከመንግስት እጅ ነጻ የሆነ የፓትርያርክ ምርጫ ፤ የተለያዩ ባለስልጣናት የጤና መታወክ ፤ በሙስሊም ማህበረሰቦች ዘንድ የተነሳው የመጅሊስ