Tuesday 31 December 2013

የአ/አ ሀ/ስብከት የአደረጃጀትና አሠራር ጥናት ካህናቱንና ምእመናኑን እያነጋገረ ነው











ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች እንዲያገልግሉ ብቻ ሳይሆን በትምህርትና በተግባራዊ ልምምድ ለከፍተኛ ክብርና ማዕርግ እንዲበቁም ትሠራለች
ገዳማት እና አድባራት የልማት ፈንድ ያቋቁማሉ
/ምንጭ፡- ኢትዮ – ምኅዳር፤ ቅጽ 02 ቁጥር 51፤ ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 23 ቀን 2006 ዓ.ም./

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰሞኑን ለሀ/ስብከቱ ባለድርሻ አካላት ለውይይት ያቀረበው የአደረጃጀትና አሠራር ጥናት ሰነድ ካህናቱንና ምእመናኑን እያነጋገረ ነው፡፡ የጥናት ሰነዱን እንደማይቀበሉት የሚገልጹ ወገኖች፡- ‹‹ጥናቱ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት ያልተሳተፉበትና በውይይት ያልዳበረ በመኾኑ በገለልተኛና ልምድ ባላቸው ምሁራን ይሰናዳ፤ ከነባሩ ሕገ ቤተ ክርስቲያንና ቃለ ዐዋዲ ጋራ የሚጋጭና የሚጣረስ ነው፤›› ይላሉ፡፡
ጥናቱ ‹‹ነባሩን ሠራተኛ በማፈናቀል በስመ ዲግሪና ዲፕሎማ ዕውቀት የሌለውን በመዋቅሩ ውስጥ በመሰግሰግ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለመቆጣጠር ያለመ ነው፤›› የሚሉት እኒሁ ወገኖች፣ ‹‹የአጥኚው አካል ማንነት በግልጽ አይታወቅም፤ በቤተ ክርስቲያኒቱ የመጨረሻ ሥልጣን ያለውን የፓትርያርኩን ሥልጣን ይጋፋል፤›› የሚሉ ተቃውሞዎችን በመዘርዘር አቤቱታቸውን ለፓትርያርኩና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት አቅርበዋል፡፡

ብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ቴዎፍሎስ

(አንድ አድርገን ታህሣሥ 21 2006 ዓ.ም)፡- 
ኢትዮጵያ ብዙ መከራዎችን አሳልፋለች ፤ ብዙዎቹ መከራዎች ከውጭ ወራሪዎች ቢደረሱም ከውስጥ ሀይሎችም ከደረሰው ጥቃት ያልተናነሰ መከራ በቤተክርስትያንና በሀገር ላይ ብዙ መከራ ደርሷል ፤ ይህች ቤተክርስቲያን ከዘመነ አክሱም ጀምሮ አሁን እስካለንበት የኢህአዴግ ዘመን ድረስ ብዙ መንግስታትን አሳልፋለች ፤ ፈሪሀ እግዚአብሔር ያላቸው ነገስታት ለቤተክርስትያን እና ለህዝበ ክርስትያን በርካታ መልካም ተግባሮችን አከናውነው ወደማይቀረው አለም አልፈዋል ፤ ስማቸውም በየዘመኑ በመልካም እየተጠራ ትውልድም የሚዘክራቸው እስከ አሁን ድረስ አሉ ፤ ሌሎች ደግሞ የምትጠፋ መስሏቸው ጦር መዘውባታል ፤ በዘመናቸው ቤተክርስትያኒቷን ለማፍረስ ድንጋይ አንስተውባታል ፤ አሳት ለኩሰውባታል ፤ እርሷ ግን የመጣውን መከራ ተቋቁማ እጃቸውን ያነሱባትን ወደ ኋላ ትታ አሁን እኛ ትውልድ ላይ ደርሳለች፡፡

Tuesday 24 December 2013

ቤተ ክርስቲያን ከ290 ሚልዮን ብር በላይ በኾነ ውጭ ሁለገብ የሥልጠና ማዕከል ልትገነባ ነው




የአደረጃጀትና አሠራር ጥናት ሰነዱ አካል የኾነው የሥልጠናና የሰው ሀብት ልማት ፖሊሲው ከአፈጻጸም ዝርዝር መመሪያው ጋራ ተዘጋጅቷል የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናታዊ ውይይቱ ተጠናቅቋል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን÷ ከአድልዎና ሙስና የጸዳ፣ ሥርዐተ እምነትዋን የሚጠብቅ፣ መንፈሳዊ ዕሴቶችዋን የሚያንጸባርቅ፣ ሞያዊ ብቃትን ማዕከል ያደረገ፣ ዘመኑን የዋጀና የተቀላጠፈ አሠራር እንዲኖራት ያስችላል የተባለ ሁለገብ የማሠልጠኛ ማዕከል ለመገንባት የፕሮጀክት ጥናቱን አጠናቅቃ ማዘጋጀቷ ተገለጸ፡፡

Monday 23 December 2013

ተግሳጽ ዘቅዱስ ዮሃንስ አፈወርቅ ክፍል አንድ በዲ/ን ህብረት የሺጥላ



‹‹እስከ አፍንጫችን ታጥቀናል›› ያሉ የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጡ ተቃዋሚዎች ከ‹‹ዶ/ር ሺፈራው ተክለ ማርያም ጋራ በየዕለቱ እየተገናኘን ነው፤ ማኅበረ ቅዱሳንን አፍርሰን ሕንፃውን እንረከበዋለን›› እያሉ ነው

‹‹ከእናንተ ጋራ መሣርያችኹ ቢኖርና በመሣርያችኹ ብትመኩም ከእኛ ጋራ ደግሞ እግዚአብሔር አለ፤ አንፈራም፤ ከዚህ በኋላ ለውጡ ወደኋላ አይመለስም፡፡›› /ብፁዕ አቡነ ሉቃስ/ የአቃቂ ቃሊቲ፣ ልደታ ቂርቆስና አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ገዳማትና አድባራት ልኡካን በጥናታዊ ውይይቱ ወቅት (ፎቶ: አዲስ አበባ ሀ/ስብከት) 

(ከሃራ ተዋህዶ)

Saturday 21 December 2013

ቤተ ክርስቲያን የካሽ ሬጅስተር ተጠቃሚ ልትኾን ነው



  • የአ/አ ሀ/ስብከት፣ የክፍላተ ከተማ ጽ/ቤቶች፣ የልማትና በጎ አድራጎት ተቋማት፣ ደረጃ አንድና ሁለት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት የቅድሚያ ተጠቃሚ ይኾናሉ
  • ለመንበረ ፓትርያርክ ማእከላዊ የፋይናንስና በጀት አስተዳደር መሠረት የሚጥል ነው
  • ምእመናን ለሚከፍሉትና ለሚሰጡት ገንዘብ ደረሰኝ የመጠየቅ ልማድ ሊኖራቸው ይገባል
  • ድብቅ ሙዳየ ምጽዋት ማስቀመጥ፣ በዣንጥላና በምንጣፍ ገንዘብ መለመን ይከለከላል

(አዲስ አድማስ፤ ታኅሣሥ ፲፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. )

Friday 20 December 2013

ምጽዋት - እዉነተኛዉ የተፈጥሮ ሚዛን

በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ

አንድ ገዳም ዉስጥ የሚኖሩ አንድ አባት አዉቃለሁ፡፡ እኝህ አባት ሁል ጊዜ የሚናገሩት በምሳሌና በተዘዋዋሪ ነዉ፡፡ በዚህ ምክንያት ለእርሳቸዉ እንግዳ የሆነ ሰዉ ነገራቸዉን ቶሎ ላይረዳዉ ይችላል፡፡ በአንድ ወቅት ከጓደኛየ ጋር ሆነን ስለ ምጽዋት ስናነጋግራቸዉ በአሁኑ ጊዜ ከጠቃሚነቱ ይልቅ ጎጂነቱ ያመዝናል የሚለዉ ሰዉ እንደሚበዛና በርግጥም ይህን ሊያስብሉ የሚችሉ ብዙ አጭበርባሪዎች መኖራቸዉን ነገርናቸዉ፡፡ እርሳቸዉም ዝም ብለዉ ካደመጡን በኋላ የሚከተለዉን ታሪክ ነገሩን፡፡ በንጉሡ ጊዜ ፈረንጆች መጥተዉ አንድ ጥያቄ አቀረቡ፡፡ ጥያቄዉም ጥቁር ነገር ለዓለማችን ጠቃሚ ስላልሆነ ከምድር ልናጠፋዉ እንፈልጋለን፤ የእርሰዎ ሃሳብ ምንድን ነዉ? የሚል ነበር፡፡ እርሳቸዉም ጎጂማ ከሆነ መጥፋት ይኖርበታል፤ ግን ጎጂነቱን አረጋግጣችኋል? ደግሞስ ምንም ሳታስቀሩ ሁሉንም ልታስወግዱ ቆርጣችሁ ተነስታችኋል ? ሲሉ ጠየቛቸዉ፡፡ እነርሱም አዎን ፤ ጥቁር ነገር ለሥልጣኔና ለመልካም ነገር እንደማይስማማ ደርሰንበታል፤ ካጠፋንማ የምናጠፋዉ ሁሉንም ጥቁር ነገር ነዉ አሏቸዉ፡፡ በዚህ ጊዜ ንጉሡም፡- ጥሩ የምትጀምሩትስ ከየት ነዉ፤ ከነጮች አገር ነዉ ወይስ ከጥቁሮች? ይላሉ፡፡ ፈረንጆቹም ሃሳባችንን እየተቀበሉት ነዉ ብለዉ እየተደሰቱ ፤ የምንጀምረዉማ በእኛ ሀገር ካለዉ ጥቁር ነገር ነዉ ሲሉ መለሱላቸዉ፡፡ እንደዚህ ከሆነና ምንም ምን የጥቁርን ትንሿንም ሳትንቁ በሀገራችሁ ካለዉ ማጥፋት የምትጀምሩ ከሆነ እስማማለሁ፡፡ ይሁን እንጂ ዐይናችሁ ዉስጥ ያለችዉንም ጥቁር ነገር ንቃችሁ መተዉ የለባችሁም፡፡ እንዲያዉም ዋናዉ የሰዉነታችሁ ክፍል ላይ በመሆኗ ከእርሷ መጀመር አለባችሁ አሏቸዉ፡፡ የሚያነጋግሯቸዉ ፈረንጆችም በዚህ ጊዜ ደንገጥ ብለዉ ለካ ጥቁር አስፈላጊ ነገር ነዉ አሉ፡፡ ይህን ከነገሩን በኋላ አባ እንደ ልማዳቸዉ ያለምንም ተጨማሪ ማብራሪያ ዝም አሉ፡፡

Tuesday 17 December 2013

''''''''''''''''''''''በጎቹና ፍየሎቹ """"""""""""

የሚከተለውን ምንባብ በጥንቃቄ አንብቡ
"""""""""""""""""""""""""""""""''''

(በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ....ምንጭ፡ሐመር የካቲት 2003 ዓ.ም. )
ከዕለታት በአንዱ ቀን በአንድ ሀገር ትልቅ የበጎች በረት ነበረ፡፡ በዚህ የበጎች በረት ውስጥ ብዙ በጎች ይኖሩ ነበር፡፡ ይህ የበጎች በረት ለረዥም ዓመት የቆየ እና ብዙ ታሪክ ያለው በረት ሲሆን በጎቹ ሁሉ ግን የሚኖሩበትን በረት ጥንታዊነት እና ታሪክ በሚገባ የሚያውቁ አይደሉም፡፡ በቅርብ ጊዜ ከሚወለዱት በጎች መካከል ለመስማት ፈቃደኞች ያልሆኑ አሉ እንጂ በረቱን እስከ ዛሬ ድረስ ጠብቆ ለማቆየት ብዙ በጎች ከሚያገሳ አንበሳ ጋር ጭምር ተታግለው ብዙ ድል አድርገዋል፡፡ ብዙ በጎችም ለዚሁ በረት መቆየት ሲሉ አንገታቸውን እስከመስጠት ድረስ ደርሰው ነበር፡፡ ከአሁኑ በጎች ውስጥ ግን አንዳንዶቹ እንኳን ራሳቸውን መሥዋዕት አድርገው ሊሰጡ የቀድሞዎቹ በጎች የፈጸሙትን ገድል እንኳን ለማመን ይከብዳቸዋል ፤ ለመስማትም ይሰለቻሉ፡፡

Monday 16 December 2013

እውን ‹‹ተሐድሶ›› የለምን?

በዲያቆን ኅብረት የሺጥላ

ሰሞኑን በተደጋጋሚ ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የለም ማኅበረ ቅዱሳን የፈጠረው ወሬ ነው!›› የሚል ንግግር በመስማቴ ይህንን አጭር ማሳሰቢያ ለመጻፍ ተነሳሣው፡፡ በእርግጥ ንግግሩን ቀደም ሲልም ሰምቼው አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን መደጋገሙ ሲበዛ በተለይም ግምት የሰጠዋቸው ሰዎች ነገሩን ተቀብለዉት ስመለከት ለካ የሚናቅ ሐሰት የለም አሰኘኝ!

‹‹ማኅበረ ቅዱሳን የፈጠረው ወሬ ነው!›› ለሚለው ለምን ፈጠረው? ይህን ሐሳብ ፈጥሮ ምን ይጠቀማል? ቢፈጥረውስ እናንተ ተሐድሶ ካልሆናችሁ ምናችሁ ይነካል? የሚል የራሴን ጥያቄ ፈጥሮ ከመጠየቅ በቀር እኔን ስለማይመለከተኝ የማኅበሩ የቤት ሥራ ነውና ራሱ ይጨነቅበት ብዬ አልፌዋለሁ፡፡ ትንሽ ማብራሪያ ለመስጠት የምሞክረው ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የለም›› በሚለው አመለካከት ላይ ነው፡፡

የሴት ራስ ወንድ

በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ

እንደምን ሰነበታችሁ፡፡ ረዘም ላለ ጊዜ በመጥፋቴ ይቅርታ እየጠየቅሁ ለጊዜዉ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የሃይማኖት ዐምድ ‹‹ሃይማኖት እና ሴቶች›› በሚለዉ የመወያያ ርእሰ ጉዳይ ላይ ከእኛ እምነት አንጻር ያቀረብኳትን ትንሽ መጣጥፍ እነሆ ብያለሁ፡፡

ቤልጄየም ዉስጥ በምትገኘዉ የአንትወርፕ ከተማ አይሁድ ይበዙባታል፡፡ በዚሁ ምክንያት በዚያ ሀገር ሱቆች እንኳ ሳይቀር በብዛት የሚይዙት ለአይሁድ የሚሆኑትን ልብሶችና ሌሎች የእነርሱን ፍላጎት የሚያሟሉ ነገሮች ነዉ፡፡ ምክንያቱም በዚያ ለሁለት ሺሕ ዐመታት በተሰደዱባቸዉ ቦታዎችም ባሕላቸዉንንና ዕሴቶቻቸዉን ጠብቀዉ የሚኖሩ በመሆናቸዉ ነዉ፡፡ የተማሩት ትምህርትና የደረሱበት ሥልጣኔና ዘመናዊነት ምንም ያህል ተጽእኖ እንዳያመጣ አድርገዉ መቛቛማቸዉም ሥልጣኔና ዕሴትን አንዴት አስታርቆ መሔድ እንደሚቻልም ምሳሌ ሊሆን ይችላል፡፡


Saturday 14 December 2013

ሰበር ዜና – ቅ/ሲኖዶስ የአፈጻጸም አቅጣጫ የሰጠበትን የአ/አ ሀ/ስብከት የመዋቅር፣ አደረጃጀትና ዝርዝር አሠራር ጥናት በመድረክ ለመሞገት አቅም ያነሳቸውና ውይይቱን ለማደናቀፍ ሲያሤሩ የቆዩ ጥቅመኛ የአጥቢያ አለቆችና የአስተዳደር ሠራተኞች በቦሌ ላሊበላ ሆቴል ኅቡእ ስብሰባ ሊያካሂዱ ነው፤ ሤረኞቹ ‹‹ይደግፉናል›› በሚል የሚነግዱባቸው አንዳንድ ሊቃነ ጳጳሳት ራሳቸውን ከሤራው እንዲያገሉና ለቅዱስ ሲኖዶሱ ውሳኔ ተፈጻሚነት እንዲቆሙ ይጠየቃሉ!!


ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምት ወር ባካሄደው የመጀመሪያ የምልአተ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ÷ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የመዋቅር፣ አደረጃጀትና የአሠራር መመሪያ ጥናት ረቂቅ በካህናት፣ በምእመናንና በሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ተሳትፎ እንዲዳብርና በቋሚ ሲኖዶሱ አማካይነት በሥራ ላይ እንዲውልበመወሰን በሰጠው የአፈጻጸም አቅጣጫ መሠረት እየተካሄደ የሚገኘውን ጥናታዊ ውይይት ለማወክ አፍራሽ ተግባራትን ሲያራምዱ የቆዩ ጥቅመኛ የአድባራት አለቆች፣ ጸሐፊዎችና የአስተዳደር ሠራተኞችበቦሌ ላሊበላ ሆቴል ኅቡእ ስብሰባ መጥራታቸው ተሰማ፡፡

Friday 13 December 2013

....የይሁዳ ሰላምታ የቀሪ ሒሳብ ማስተካከያ ነው!!


ከብርሃን ብሂል
ከፌስቡክ ገጿ ላይ የተወሰደ

ሰሞኑን ከሀዋሳ ንፋስ ማዶ አንድ ወሬ ሰማን እነ……….ይቅርታ ጠየቁ አሉii
ማንም ሰው ስለበደሉ ይቅርታ መጠየቁ አጀብ የሚያሰኝ የሚያስመሰግንም ነው፡፡ ስንፀልይም “…..የበደሉንን ይቅር እንደምንል….. እንል የለ? ግን የሰዎቹ ጥፋት የሰው ነው ወይስ የሃይማኖት?(ሰዎቹ የበደሉት የሀዋሳን ምእመን ነው ወይስ ሃይማኖታችንን)? ታዲያ የሃይማኖት በደል በጉልበት(በሰዎች ፊት) በመንበርከክ ይቅርታ ይባላል እንዴ? የሰው በደልስ ቢሆን ልብ ካልተንበረከከ ጉልበት ቢንበረከክ ምን ዋጋ አለው፡፡ የሃይማኖት በደል ግን በኃያሉ በእግዚአብሔር ፊት እራስን አዋርዶ በንስሃ በመመለስ፣ በቀኖና ቤተክርስቲያን፣ በእግዚአብሔር ቃል…. ሂድና እራስህን ለካህን አሳይ…. እንጂ፡፡


Tuesday 10 December 2013

ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን የወጡ (ያፈነገጡ) ሰዎች የሚመለሱት እንዴት ነው? በ(ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ)

December 11, 2013
በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ (ከፌስቡክ ገጹ ላይ የተወሰደ)

፩. የቤተ ክርስቲያን ምንነት፣ ዓላማና ተልእኮዎች

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምትባለው በአጭር ቃል የኢየሱስ ክርስቶስ አካል ስትሆን፣ አማንያን ደግሞ የተለያዩ የአካል ክፍሎቿ ናቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ባለቤቷና መሥራቿ እግዚአብሔር ሲሆን ከእግዚአብሔር ጋር መንፈሳዊ ኅብረትና ግንኙነት ያላቸው መንፈሳውያን አንድነት (ጉባኤ) ናት፡፡ አንድ ሰው በሃይማኖትና በምሥጢራት አማካይነት ወደዚህች ጉባኤ ሲገባ የዚህ ጉባኤ (ኅብረት) አካል ሆኖ ይሠራል፡፡ ሐዋርያው “ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር የታመነ ነው” በማለት ያስረዳው ይህን ነው፡፡ 1 ቆሮ. 1፡9 እንዲሁም “ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም” የሚለው ቃል ይህን የቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊ እሳቤ ያሳያል። ኤፌ. 2፡19-22 ይህች እግዚአብሔር የመሠረታት ጉባኤ (ማኅበር) ቀዳማዊት ናት፤ “ተዘከር ማኅበረከ ዘአቅደምከ ፈጢረ - አስቀድመህ የፈጠርሃትን ማኅበርህን አስብ” ያለው ለዚህ ነው፡፡ መዝ. 73፡2

የቤተ ክርስቲያን የአንድነቷ መሠረት ሃይማኖት ነው፡፡ ይህ ሃይማኖት ደግሞ ከእግዚአብሔር የተሰጠ አንድና ብቸኛ እውነት ነው፡፡ ሐዋርያው “ብዘገይ ግን፥ በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት እንዴት መኖር እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፤ ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው” ያለው ለዚህ ነው፡፡ 1 ጢሞ. 3፡15 ይህ የቤተ ክርስቲያን አምዷ (ምሰሶዋ) የሆነው እውነትና ሃይማኖት ካልተጠበቀ ወይም ችላ ከተባለና እግዚአብሔር ከገለጠው እውነት ጋር እንሸቃቅጠው ከተባለ ቤተ ክርስቲያን ባሕርይዋ ስለማይፈቅድላት እንዲህ ያለ ነገር መቀበል አትችልም፡፡ የቤተ ክርስቲያን መሠረቷ እና ዓምዷእውነት ነውና፡፡

የመስቀል ደመራ ክብረ በዓል የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የዓለም መንፈሳዊ ቅርስ ኾኖ በዩኔስኮ ተመዘገበ

December 5, 2013 
(ሪፖርተር፤ ኅዳር ፳፮ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.)

ኄኖክ ያሬድ



የኢትዮጵያው የመስቀል ክብረ በዓል በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ዩኔስኮ አስታወቀ፡፡ ዩኔስኮ የመስቀል ክብረ በዓልን (Commemoration feast of the finding of the True Holy Cross of Christ) በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ኅዳር 25 ቀን ይፋ ያደረገው፣ በኢንታንጀብል (መንፈሳዊ) ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃና ክብካቤ ላይ የሚሠራው ኮሚቴው ስምንተኛውን ጉባኤ እያካሄደባት ካለው የአዘርባጃኗ ባኩ ከተማ ነው፡፡

Monday 9 December 2013

በፔርሙዝ ተለውጦ አሜሪካ የተሻገረው የ400 ዓመቱ ብራና


08 December 2013 
ተጻፈ በ ፍቅር ለይኩን
(ከአንድ አድርገን ድረ-ገጽ ላይ የተወሰደ)

የቅርሶቻችን ዋጋ ምን ያህል ነው?

(ሪፖርተር ጋዜጣ):- የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ)...በዓለም ጥንታዊ ቅርስነትከመዘገባቸው የሥነ ጽሑፍ ውጤቶች መካከል በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ባለቤትነት የተመዘገቡና በብራና ላይ የተጻፉ የመጽሐፍቅዱስ ክፍሎች የነገረ ሃይማኖት ጽሑፎች ይገኙበታል፡፡

እነዚህ እስከ ሺሕ ዓመታት ዕድሜን ያስቆጠሩ ብርቅና ውድ የሆኑየሥነ ጽሑፍ ቅርሶች በተለያዩ ጊዜያት በአገሪቱ በደረሱ ተፈጥሮአዊናሰው ሠራሽ አደጋዎች ምክንያት ውድመት፣ ጥፋትና ዝርፊያእንዳጋጠማቸው ይታወቃል፡፡ከዚህም በተጨማሪ በጥናትና በምርምር ሰበብ ከአገር የወጡ ጥንታዊ ብራናዎች አያሌ ናቸው፡፡በአውሮፓና በአሜሪካ በሚገኙ ትላልቅ ዩኒቨርሲቲዎችና አብያተ መጻሕፍት፣ እንዲሁም በግለሰቦች፣ በቅርስ አሻሻጮች እጅም ማግኘትየተለመደ ነው፡፡

Monday 25 November 2013

………... ጾምን ቀድሱ ………….
                                                                                                                     በገጣሚ ልዑል ገ/እግዚአብሄር
                                                                                                                     ከፌስቡክ ገጹ ላይ የተወሰደ


የሥጋ አውታሩ በዝንጥል ይመታል 
ዕለታዊ ምቱ .... በሆድ ተጎብኝቷል 
አፍለኛ ንጣቴን ሽበት አድክሞታል 
በሥጋ ላይ በዝቶ ሥጋን አግምቶታል!

ሆዴን ሳበዛበት “ልተኛ ልተኛ” ይለኛል 
ሸክሙን ስነሳው .... ተጣፍቶ ይቀለኛል 
ያ ልብላህ ያልሁት ሥጋ ጥርስ ሰርቶ ነክሶኛል 
በስድሳ ሰማንያ ሸውዶ ...... መቃብር ከቶኛል! 

Tuesday 5 November 2013

ሰኮናቸው ያልተሰነጠቀና የማያመሰኩ እንስሳት (የዘመናችን ተሐድሶዎች)(የመጨረሻ ክፍል)

ሠለስቱ ደቂቅን ያዳናቸው ማን ነው ?
በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ

ታዲያ ሠለስቱ ደቂቅን ያወጣቸው ማን ነው? ለሚለው የተሐድሶዎች ጥያቄ የቀረበ መልስ
መጀመሪውንም መጽሐፍ ቅዱሱ ገብርኤል ነው አይልም፡፡ መጽሐፍ ቅዱሱ የሚለው የሚከተለውን ነው፤ ‹‹ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ አማካሪዎቹንም፤ ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን? ብሎ ተናገራቸው። እነርሱም፦ ንጉሥ ሆይ፥ እውነት ነው ብለው ለንጉሡ መለሱለት። እርሱም፦ እነሆ፥ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል ብሎ መለሰ ›› /ዳን 3 ፤ 24 -25/ ፡፡ በዚህ ገለጻ መሠረት አራተኛውን ያየው ንጉሡ ናቡከደነጾር ነው፡፡ እርሱም አየሁ ያለው አራተኛ ሰው ነው፡፡ የጨመረበት ቢኖር አራተኛው የአማልክትን ልጅ ይመስላል የሚለውን ነው፡፡ ለመሆኑ አራተኛውን ሰው እርሱ ብቻ ለምን አየ ? ሌሎቹ ለምን አላዩም ? አንደኛው የጥያቄው ቁልፍ ምስጢር ያለው እዚህ ላይ ነው፡፡ እውነቱን ለመናገር ይህ ሰው ጥንቱንም ሠለስቱ ደቂቅን ወደ እሣት የጣለው ራሱን ምስል አቁሞ ለምስሉ ሕዝቡን በማሰገድ ራሱን አምላክ አድርጎ ሊያስመልክ ነበር፡፡ ታዲያ ራሱንና እርሱን የመሰሉትን አምላክ አድርጎ የሚቆጥር ከሆነ የሚያየውን አራተኛውን ሰው ‹‹ የእኛን ልጅ ይመስላል ወይም እኛን ይመስላል›› ለምን አላለም? ከዚያ ይልቅ አርቆ ሌሎች አማልክትን የሚያመልክ አስመስሎ ‹‹ የአማልክትን ልጅ›› ይመስላል ያለበት ምስጢር ምንድን ነው ? ይህን ያለበት ምክንያቱ ያየው ነገር አራተኛው አካል ከህልውና ያለው በዘር በሩካቤ የተወለደ ሰው እነርሱ ሳያዩት እሳቱ ውስጥ ገብቶ ሳይሆን ነገሩ መገለጥ ስለሆነ ነው፡፡

የሌለውን ፍለጋ - ክፍል ሁለት (ለተስፋዬ ገ/አብ የተሰጠ ምላሽ)

በዲ/ን ዳንኤል ክብረት

በይምርሐነ ክርስቶስ ጣራ ላይ የሚገኘው የዳዊት ኮከብ

ባለፈው ሳምንት ተስፋዬ ገብረ አብ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ያነሣቸውን ነጥቦች ማየት ጀምረን ‹የሦስቱን ተክለ ሃይማኖቶች› ጉዳይ ለዛሬ አቆይተነው ነበር፡፡ እንቀጥል፡፡

1) የሰባተኛው መክዘ ተክለ ሃይማኖት

ተስፋዬ የጠቀሳቸው የሰባተኛው መክዘ ተክለ ሃይማኖት የሉም፡፡ እስካሁንም እንደርሱ ፈጠራቸውን የሚናገሩ እንጂ ማስረጃ ያመጡ አልተገኙም፡፡ ይህንን ነገር መጀመሪያ ያነሣው የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ገድለ ተክለ ሃይማኖትም ስለ ጽላልሽ (ኢቲሳ) ተክለ ሃይማኖት እንጂ ስለ ሰባተኛው መክዘ ሌላ ተክለ ሃይማኖት አይናገርም፡፡ ገድለ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ልዩ ልዩ ቅጅዎች ቢገኙም ሁሉም ግን በተወለዱበት ቦታ፣ በተወለዱበት ዘመን፣ በወላጆቻቸው ስም፣ በሠሯቸው ሥራዎችና በገዳማቸው ላይ የሚተርኩት ታሪክ ተመሳሳይ ነው(Encyclopedia Aethiopica, Vol., IV,.P.833) በአንድ ወቅት ታላቁን የታሪክና የኢትዮጵያ ጥንታውያን መዛግብት ሊቅ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌን ስለዚህ ጉዳይ ስጠይቃቸው ‹አለኝ ያለ ማስረጃውን ያምጣ፣ የለም የምንለው ፈልገን ልናመጣ አንገደድም›› እንዳሉት አለን የሚሉት እስኪያመጡ ድረስ የምናውቀውን ይዘን እንቀጥላለን፡፡

Sunday 3 November 2013

ሰኮናቸው ያልተሰነጠቀና የማያመሰኩ እንስሳት (የዘመናችን ተሐድሶዎች)

ሠለስቱ ደቂቅን ያዳናቸው ማን ነው ለሚለው የተሐድሶዎች ጥያቄ የቀረበ መልስ
በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ

ሰሞኑን በተለይ በርከት ባሉት በመጽሐፈ ገጽ ወዳጆቼ በኩል  ‹‹ ሠለስቱ ደቂቅን ያዳናቸው ማን ነው? ›› የሚል ጥያቄ በተደጋጋሚ ቀርቦልኛል፡፡ በተሐድሶዎች በተሰራጨ አንድ የቪዲዮ ቁራጭ ላይ በሦስቱ ድርሳናት ማለትም በድርሳነ ገብርኤል ላይ ገብርኤል ፤ በድርሳነ ሚካኤል ላይ ሚካኤል ፤ በድርሳነ ራጉኤል ላይ ደግሞ ራጉኤል አዳናቸው ተብሎ ስለተገለጸ ትክክሉ የቱ ነው፤ በርግጥ ያዳናቸውስ ማን ነው የሚል ነው፡፡ በዚያም ጊዜ ሆነ ዛሬ ከአንዳንዶቹ መልእክት እንደተረዳሁት የድንጋጤ ስሜትም የተሰማቸው አሉ፡፡ ይህን ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊቶችንም ስመለከት ለጉዳዩ ቢያንስ አንዲት ትንሽ መጣጥፍ እንዳአቅሜ  እንኳ ለጊዜው መስጠት እንዳለብኝ ስለተሰማኝ ጥያቄውን ለላካችሁልኝ ሁሉ ይህችን መቆያ እንካችሁ ብያለሁ፡፡ ዋናው ወይን ሁልጊዜም ወደ ኋላ መምጣቱ አይቀርምና እርሱን አብረን ከወይን አዳዩ እንጠብቃለን፡፡

ከላይ ያነሣሁትንና ሌሎች ተመሳሳይ ጉዳዮች ብዙ ጊዜ የሚረብሹን ለምንድን ነው ብየ ሳስብ ብዙዎቻችን ወግ ባለውና ለእኛ በሚሆን መንገድ አለመማራችን የመጀመሪያውን ስፍራ ሊይዝ ይችላል፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ  ደግሞ በዚህ ጽሑፍ በዋናነት የምንመለከተውን የመሰሉ ጥያቄዎች እያነሡ ገድላትን፤ ድርሳናትንና ሌሎች አዋልድንም የሚነቅፉና የሚያጸይፉ ሰዎች ቁጥራቸው በርከት እያለ መጥቷል፡፡ ከዚህም የተነሣ በተለያዩ ሚዲያዎች የተለያዩ ጽሑፎችና የምስል ወድምፅ ስብከቶች ይቀርባሉ፡፡ በዚህም ስለቅዱሳት መጻሕፍት ትርጓሜ ወይም ምሥጢራት ግንዛቤያችን አነስተኛ የሆነብንን ሰዎች በትንሹም ቢሆን ሊረብሸን ይችላል፡፡እኔም ዝም ብየ በአንዲት ብጣሽ ጉዳይ ላይ ብቻ እንዲህ ነው ወይም እንዲያ ነው ከማለቴ በፊት ነገሩን ከመሠረቱ ለመረዳት እንዲያመቸን ቅዱሳት መጻሕፍት ላይ የሚነሡ ጥያቄዎችን ብቻ ሳይሆን የማንጠየቃቸውንም በአግባቡ ተረድተን እንድንጠቀም የሚረዳውን መንገድ ጠቆም ላድርግ፡፡ ስለዚህ አስቀድመን ቅዱሳት መጻሕፍትን እንዴት ልንረዳ እንደምንችል ላቅርብና በሚቀርበው ጥያቄ ሁሉ ሳንረበሽ መልሱን እንድንጠብቅ ለማመላከት ልሞክር፡፡

Thursday 31 October 2013

ተሀድሶያውያን ‹‹ ቅዱስ አትናቴዎስ የወንጌል አገልግሎት›› የሚል የእምነት ተቋም ሊያቋቁሙ ነው

(አንድ አድርገን ጥቅምት 21 2006 ዓ.ም)፡- THE ETHIOPIAN HERALD TUESDAY 29 OCTOBER 2013 ዕትም ገጽ 7 ላይ ይህን ነገር ይዞ ወጥቷል ፡፡

Notice 

“KIDUS ATNATEWOS YEWENGEL AGELEGELOT” has applied use this name as a religious institution. Any individual or organization opposing the name is here by requested to report to the Ministry of Federal Affairs and Religious Organization and Association Registration directorate, Office on November 11/2013 at 9:00 AM

Ministry of Federal Affairs
Notice
“KIDUS ATNATEWOS YEWENGEL AGELEGELOT” has applied use the under indicated symbol.


(ቅዱስ አትናቴዎስ የወንጌል አገልግሎትየሚል መስቀል ያለው ክብ ምልክት)Any individual or organization opposing the symbol is here by requested to report to the Ministry of Federal Affairs and Religious Organization and Association Registration directorate, Office on November 11/2013 at 9:00 AM
Ministry of Federal Affairs

ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት በዲ/ን ህብረት የሺጥላ Yihen Lemetasebiaye Aderegut by D/n Hibret Yeshitela



Wednesday 30 October 2013

የሌለውን ፍለጋ -ክፍል አንድ

በዳንኤል ክብረት


አቡነ ተክለ ሃይማኖትና አቡነ ኤዎስጣቴዎስ( ጎርጎራ፣ ደብረ ሲና ማርያም)

ተስፋየ ገብረ አብ ‹የስደተኛው ማስተዋሻ› የተሰኘ መጽሐፍ ማውጣቱንና ባነበው መልካም እንደሆነ ገልጦ አንድ ወዳጄ ‹ስስ ቅጅውን› ከሀገረ አሜሪካ ላከልኝ፡፡ ከዚህ በፊት ሌሎች መጻሕፍቱን አንብቤያቸዋለሁ፤ በአጻጻፍ ችሎታው የምደሰተውን ያህል እንደ አበሻ መድኃኒት ነገሩን ሁሉ እርሱ ብቻ የሚያውቀው ምስጢር ስለሚያደርገው፤ በአንዳንድ ጉዳዮችም ሆን ብሎም ሊያናጋቸው የሚፈልግ ኢትዮጵያዊ እሴቶች ያሉ ስለሚመስለኝ፤ ተስፋዬ ለምን እንደዚህ ይጽፋል? እያልኩ የምጠይቃቸው ነገሮች ነበሩ፡፡

በዚህ መጽሐፉ ውስጥም ያንን ጥርጣሬየን አጉልቶ ሥጋ ነሥቶ እንዳየው የሚያደርገኝ ነገር ገጠመኝ፡፡ ተስፋየ በገጽ 306 ላይ ‹‹የፍስሐ ጽዮን ፖለቲካ› በሚል ርእስ ስለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የማያውቀውን ነገር ጽፏል፡፡ ስለማያውቀው ነገር የጻፈው ባለማወቁ ብቻ አይመስለኝም፡፡ አንድም ለማወቅ ባለመፈለጉ፣ አለያም ሆን ብሎ የማፍረስ ዓላማ ይዞ ይመስለኛል፡፡
ይህን የምለው በሁለት ምክንያት ነው፡፡ ተስፋዬ ስለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለመጻፍ ሲፈልግ ሊያነባቸው የሚችላቸው መጻሕፍት በምድረ አውሮፓ እንደ ማክዶናልድ በዝተው ሞልተው ይገኛሉ፡፡ አብዛኞቹ ደግሞ ኢትዮጵያውያን ባልሆኑ ሰዎች የተጻፉ ናቸው፡፡ ሌላው ቢቀር ኤንሪኮ ቼሩሊ የደብረ ሊባኖስ አበ ምኔቶች ታሪክ(Gli Abbati di Dabra Libanos, 1945)፣ ኮንቲ ሮሲኒ ከሐተታ ጋር ያሳተመውን ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፣በዋልድባ ቅጅ (Il Gadla Takla Haimanot secondo la redazione Waldebbana, 1896)፣ የዊልያም በጅን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሕይወትና ተአምር (The Life and Miracles of Takla Haymanot, 1906)፡፡ ከኢትዮጵያውያን ጸሐፍትም ውስጥ የታደሰ ታምራትንChurch and State in Ethiopia, ማንበብ በተገባው ነበር፡፡

Monday 7 October 2013

ቀጣዩ የኢሕአዴግ ዒላማ ማኅበረ ቅዱሳን ይኾን?

FACT Weekily Magazine cover story


(ፋክት መጽሔት፤ ቅጽ 2 ቁጥር 14 መስከረም ፳፻፮ ዓ.ም.

ተመስገን ደሳለኝ

የኢሕአዴግ ታጋዮች የመንግሥት ‹‹ጠንካራ ይዞታ›› የሚባሉ ከተሞችን ሳይቀር መቆጣጠር ችለዋል፤ ወደ አዲስ አበባም የሚያደርጉት ግሥጋሴም ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያምን ሳይቀር ዕንቅልፍ ነስቷል፡፡ በአንዳች ተኣምር ግሥጋሴውን መግታት ካልቻሉ በጥቂት ወራት ውስጥ ሁሉም ነገር ታሪክ እንደሚኾን በማወቃቸው መላ በማፈላለጉ ላይ ተጠምደዋል፡፡ በዚህን ጊዜ ነበር(የሐሳቡ አመንጪ ተለይቶ ባይታወቅም)፣ ‹‹ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አጭር ሥልጠና ሰጥቶ ከሀገሪቱ ሠራዊት ጎን ማሰለፍና የ‹ወንበዴውን ጦር› መድረሻ ማሳጣት›› የሚለው ሐሳብ እንደ መፍትሔ የተወሰደው፡፡

እናም መንግሥቱ ራሳቸው ተማሪዎቹን በዩኒቨርስቲ አዳራሽ ሰብስበው እንዲህ ሲሉ አፋጠጧቸው፡- ‹‹እነርሱ (ኢሕአዴግና ሻዕቢያን ማለታቸው ነው) ለእኵይ ዓላማቸው ከእረኛ እስከ ምሁር ሲያሰልፉ እናንተ ምንድን ነው የምትሠሩት? በሰላማዊ ሰልፍና በስብሰባ ብቻ መቃወም ወይስ ወንበዴዎቹ እንዳደረጉት ከአብዮታዊ ሠራዊታችነ ጎን ቆማችኹ የአገሪቱን ህልውና ታስከብራላችኹ?››

ይህን ጊዜም አስቀድሞ በተሰጣቸው መመሪያ ከተማሪው ጋራ ተመሳስለው በአዳራሹ የተገኙት የደኅንነት ሠራተኞችና የኢሠፓ ካድሬዎች ‹‹ዘምተን ከጠላት ጋራ መፋለም እንፈልጋለን›› ብለው በስሜትና በወኔ እየተናገሩ በሠሩት ‹ድራማ› ተማሪው ትምህርት አቋርጦ እንዲዘምት ተወሰነ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲም ተዘጋ፤ ተማሪዎቹም ለወታደራዊ ሥልጠና ደቡብ ኢትዮጵያ ወደሚገኘው የብላቴ አየር ወለድ ማሠልጠኛከተቱ፡፡

ከመላው ዘማቾች [የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ የኾኑ ሠልጣኞች በማሠልጠኛው ባዶ ድንኳን] በየጊዜው እየተሰበሰቡና በመጨረሻም ካምፓቸው አቅራቢያ ወደሚገኘው ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ከመዐቱ ይታደጋቸው ዘንድ ፈጣሪያቸውን በጸሎት መማጠን የሕይወታቸው አካል አደረጉት፤ ከቀናት በኋላም በአንዱ ዕለት አንድም ለመታሰቢያና ለበረከት. ሁለትም ስብስቡ ሳይበተን ወደፊት እንዲቀጥል በሚል ዕሳቤ ‹‹ማኅበረ ሚካኤል›› ብለው የሠየሙትን የጽዋ ማኅበር መሠረቱ፡፡ . . . ይኹንና ከመካከላቸው አንዳቸውም እንኳ በ፲፱፻፸፯ ዓ.ም በፓዌ መተከል ዞን የተደረገውን የመልሶ ማቋቋም ሠፈራ ፕሮግራም እንዲያመቻቹ በዘመቱ ተማሪዎች ከተመሠረተውና ከተለያዩ የጽዋ ማኅበራት ጋራ በመዋሐድ የዛሬውን ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› እንደሚፈጥሩ መገመት የሚችሉበት የነቢይነት ጸጋ አልነበራቸውም፤ የኾነው ግን እንዲያ ነበር፡፡

Wednesday 2 October 2013

ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን የወጡ (ያፈነገጡ) ሰዎች የሚመለሱት እንዴት ነው?

ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ
(ከማኅበረ ቅዱሳን ድህረ ገጽ ላይ ሳይቀነስ ሳይጨመር  የተወሰደ)


፩. የቤተ ክርስቲያን ምንነት፣ ዓላማና ተልእኮዎች

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምትባለው በአጭር ቃል የኢየሱስ ክርስቶስ አካል ስትሆን፣ አማንያን ደግሞ የተለያዩ የአካል ክፍሎቿ ናቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ባለቤቷና መሥራቿ እግዚአብሔር ሲሆን ከእግዚአብሔር ጋር መንፈሳዊ ኅብረትና ግንኙነት ያላቸው መንፈሳውያን አንድነት (ጉባኤ) ናት፡፡ አንድ ሰው በሃይማኖትና በምሥጢራት አማካይነት ወደዚህች ጉባኤ ሲገባ የዚህ ጉባኤ (ኅብረት) አካል ሆኖ ይሠራል፡፡ ሐዋርያው “ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር የታመነ ነው” በማለት ያስረዳው ይህን ነው፡፡ 1 ቆሮ. 1፡9 እንዲሁም “ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም” የሚለው ቃል ይህን የቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊ እሳቤ ያሳያል። ኤፌ. 2፡19-22 ይህች እግዚአብሔር የመሠረታት ጉባኤ (ማኅበር) ቀዳማዊት ናት፤ “ተዘከር ማኅበረከ ዘአቅደምከ ፈጢረ - አስቀድመህ የፈጠርሃትን ማኅበርህን አስብ” ያለው ለዚህ ነው፡፡ መዝ. 73፡2

የቤተ ክርስቲያን የአንድነቷ መሠረት ሃይማኖት ነው፡፡ ይህ ሃይማኖት ደግሞ ከእግዚአብሔር የተሰጠ አንድና ብቸኛ እውነት ነው፡፡ ሐዋርያው “ብዘገይ ግን፥ በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት እንዴት መኖር እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፤ ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው” ያለው ለዚህ ነው፡፡ 1 ጢሞ. 3፡15 ይህ የቤተ ክርስቲያን አምዷ (ምሰሶዋ) የሆነው እውነትና ሃይማኖት ካልተጠበቀ ወይም ችላ ከተባለና እግዚአብሔር ከገለጠው እውነት ጋር እንሸቃቅጠው ከተባለ ቤተ ክርስቲያን ባሕርይዋ ስለማይፈቅድላት እንዲህ ያለ ነገር መቀበል አትችልም፡፡ የቤተ ክርስቲያን መሠረቷ እና ዓምዷእውነት ነውና፡፡

Friday 6 September 2013

ስብሓት ነጋ ጥፋቷን ስለሚመኙላት ቤተ ክርስቲያንና መግደያ ብትር ሊያደርጉት ስለሞከሩት ማኅበረ ቅዱሳን ይወተውታሉ

‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የሚያስተኛ አይደለም
/አቶ ስብሓት ነጋ/
(ኢትዮ-ምኅዳር ቅጽ 01 ቁጥር 34፤ ረቡዕ ነሐሴ ፳፱ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም.)
የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋራ በመተባበር በአዲስ አበባ በአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ ከነሐሴ ፳፩ – ፳፪ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. ‹‹የሃይማኖቶች በሰላም አብሮ የመኖር እሴት በማጎልበትና ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌዎችን በማክበር የሀገራችንን የሕዳሴ ጉዞ ለማሳካት እንረባረባለን›› በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ጉባኤ ላይ ‹አቦይ› ስብሐት ነጋ በመገኘት አነጋጋሪ ሐሳቦችን ሰንዝረዋል፡፡ አንጋፋው የህወሓት/ኢሕአዴግ መሥራችና የጀርባ ሰው የሚገልጹት ሐሳብ የመንግሥትን ቀጣይ ርምጃ ያመላክታል በሚል በአጭሩ እንደሚከተለው 
አክራሪነት ይዘቱ ሃይማኖታዊ እንዳልኾነ ሕዝቡም የተገነዘበው ጉዳይ መኾኑ ተደጋግሞ ተገልጧል፡፡ ሃይማኖትን የፖሊቲካ መድረክ የሚያደርጉት የሽብርተኝነት ተግባር ለመፈጸም መኾኑ ግልጽ የኾነልን ይመስለኛል፡፡
አክራሪነትና ጽንፈኝነት በሃይማኖት ውስጥ ማስገባት የመጀመሪያው አደጋ ሲኾን በዚህ ኹኔታ ሃይማኖቱም ሃይማኖት አይኾንም፡፡ አማኞች፣ አክራሪነትና ጽንፈኝነት በየሃይማኖታቸው ውስጥ ሲታይ ሃይማኖታቸው አደጋ ላይ እንደወደቀ መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡
አቶ ካሳ ተክለ ብርሃን (የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ) እንዳለውም፣ በጣም አስደናቂ የኾነውን የኢትዮጵያ ዕድገት ማደናቀፍ ከማንኛውም ወንጀል በላይ በሕዝብ ላይ ከባድ ወንጀል መፈጸም ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለብዙ ዓመታት ሲሠቃይ የነበረ በመኾኑ አሁንም ሕዝቡን ለሥቃይ መዳረግ ተወዳዳሪ የሌለው ወንጀል ነው፡፡
በማንኛውም ሃይማኖታዊ አክራሪነት እና ጽንፈኝነት፣ በምንም ዐይነት ኹኔታ አንድም ሰው ለአንድ ደቂቃ እንኳ ተዘናግቶ መተኛት የሌለበት ሲኾን በተለይ ይህን ነገር በጥብቅ በሁሉም መንገድ መታገል አለብን፡፡
አሁን በኢትዮጵያ ያለውን ዕድገት የሚቀናቀነው የውጭ ተቀናቃኝ ነው፡፡ የእነዚህን ተቀናቃኞች ዓላማ በመያዝ በአክራሪነትና በጽንፈኝነት መልክ ታላቅ ክሕደት መፈጸም ከባድ አገራዊ ክሕደት ነው፡፡ የውጭ ጠላት ቀላል ስላልኾነ አንድም ሰው ሳይቀር በጣም ተጠናክረን መመከት ይገባል፡፡ ሕገ መንግሥቱን መሠረት ያደረገ የፖሊቲካ ልዩነት ሊኖር ይችላል፤ ሕገ መንግሥቱን የመጣስ ዝንባሌ ግን እጅግ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ መንግሥቱ ብዙ ዋጋ ተከፍሎበታል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያጸደቀው የራሱ ሕገ መንግሥት ስለኾነ ሕዝብ በመራራ ትግል ያጸደቀውን ሕገ መንግሥት መጣስ የወንጀሎች ሁሉ ወንጀል ነው፡፡
በዚህ ስብሰባ ከፍተኛ ግንዛቤ መያዙ በጣም የሚያስደስት ነው፤ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ታላቅ ተስፋ ነው፡፡ ለውጭ ጠላት ደግሞ ሲጠብቀው የነበረ ብጥብጥ መቅረቱ ሕዝብን የሚያስደስት፣ ጠላትን ደግሞ የሚያሳፍር ነው፡፡

Friday 23 August 2013

በቄሣራውያን መዳፍ ሥር ያለ አስኬማ -ክፍል(2)

በታደሰ ወርቁ ከፌስ ቡክ ገጹ ላይ የተወሰደ


ቋማዊ ለውጥ (Institutional Reform) የተቋማዊ ቀውስ መድኀን የመሆኑን ያህል  ፤ውጤታማ ያለመሆኑም ተግብሮት የተቋማዊ ውድቀት አመክንዮም ነው፡፡የተቋማዊ ውድቀቱ አመክንዮም ተቋሙ ከቆመለት መሠረታዊ ግብ-ዓላማ-ተልእኮ ጋራ ሰለሚቆራኝ ክትያው ተቋማዊ ቁመናን አሳጥቶ የታሪክ ሽታ ከመሆን የዘለለ ፋይዳ እንይኖረው ያደርጋል ፡፡ ከአምስተኛው ፓትርያርክ ሞት በኃላ በተቋማዊ ለውጥ ጅምሮች ላይ ተስፋ ያደርግነው በአንድ ጀንበር የቤ ተክህነቱ ተቋማዊ የሞራል ዝቅጠት ፈውስ ያገኛል በሚል ሳይሆን የተቋማዊ ውድቀትን አመክንዮ ተግብሮት ቀድሞ ከመረዳት ነው፡፡ከዚህ አኳያ በቤተ ክህነቱ ላዕላይና ታህታይ መዋቅር መምጣት ያለበት ተቋማዊ ለውጥ በሁለት ዳርቻዎች ሊጠቃለል ይችላል፡፡በመጠን ለውጥ (Quantitative Change)እና በዐይነት ለውጥ (Qualitative Change)፡፡   

ባለፈው ዕትም  በዚሁ ርዕስ ከአምስተኛው ፓትርያርከ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎሰ ሞት በኃላ ተስፋ ያደርግነው በድዩስጶራነት በሚኖሩ አባቶች እና በቅዱስ ሲኖዶስ መካከል ሲደረግ የነበረው የእርቀ ሰላም ድርድር እንዴት እና በምን መልክ እንደመከነ በዝርዝር ተመልክተናል፡፡በዚህ ዕትም  የምንመለከታቸው ሁለት የመከኑ ተስፋዎችና ተግብሮታዊ ክትያዎቻቸውን እነሆ፡፡
የተቋማዊ ለውጥ ጅምሮች!                              

                                      

የትኛውም ለውጥ በመጠን  ለውጥ  ላይ የተመሠረተ  ወይም ከሱ እንደሚመነጭ የለውጥ ኀልዩት ያስረዳል፡፡ከቤተ ክህነቱ አኳያ የመጠን ለውጥ መምጣት አለበት ሲባል  ቤተ ክርሰቲያኒቱ የመሠረተ እምነት ፣የሥርዐት አምልኮና ትውፊት ለውጥ ሳታደርግ ፤እነዚህኑ ተቋማዊ ዓምዶቿን ከኢትዮጵያውያን መጠነ ክበብ ወደ ቀረውም ዓለም ማስፋትየሚያስችሏትን  ፖሊስዎች፣ስትራቴጂዎችና መዋቅራዊ አደረጃጀቶችን መፍጠር አለበት ማለት ነው፡፡                                                                       

 በሌላ በኩል ደግሞ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረትነት  በመሠረተ እምነቷ፣በሥርዐተ አምልኮዋና በትውፊቷ ላይ ቅሰጣ የሚፈጽሙትን ቡድኖችና ግለሰቦች አውግዞ መለየት የሚያስችል ብቁና ፈጣን ድርጅታዊ ድርጁነት መፍጠር መቻልም የመጠን ለውጥ አንዱ ዘርፍ ነው፡፡       
  

Thursday 22 August 2013

በቄሣራውያን መዳፍ ሥር ያለ አስኬማ(ክፍል-1)

በታደሰ ወርቁ ከፌስ ቡክ ገጹ ላይ የተወሰደ


ይህ ጹሑፍ በእነ ተመስገን ደሳለኝ -ፋክት መጽሔት ላይ በሁለት ተከታታይ ክፍል የወጣ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አምስተኛ ፓትርያርክ የነበሩት እና በአዛጋቢነታቸው የሚታወቁት ብፁዕ ወቅዱስ  አቡነ ጳውሎስ ቅጥ በአጣው አምባገነናዊነታቸው የተነሣ በቅጡ ሳይዘከሩና አስክሬናቸውም ያረፈበት ስፍራም ለመዓርጋቸውም ሆነ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ክብር በማይመጥን መልክ በቆርቆሮ እንደታጠረ  እነሆ የሙት ዓመት መታሰቢያቸው ዋዜማ ላይ እንገኛለን፡፡                                                                                                ቅዱስነታቸው የሙት ዓመት መታሰቢያ ዋዜማ ላይ መሆናችንን ከተገነዘብን ሦስት መሠረታዊ ጥያቄዎችን ማንሳታችን አይቀርም፡፡ የመጀመሪያው ተሰያሚው ፓትርያርክም ሆኑ ጳጳሳቱ ከአምስተኛው አወዛጋቢ ፓትርያርክና ከዘመነ ፕትርክናቸው ውድቀት ምን ተምረው ምን አደረጉ ? የሚለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ  የቅዱስነታቸውን ሞት እንደ አንድ  ምቹ አጋጣሚ በመቁጠር በቀኖና ተጥሷል-አልተጣሰም ጭቅጭ የተነሣ የተከፈለውን የቤተ ክርስቲያኒቱን መዋቅራዊ አሐቲነት ለማከም ምንድ ተደርጉነው ውጤቱ እንዲህ የከፋው? የሚለው ነው፡፡  ሦስተኛው  ከአምስተኛው ፓትርያርክ ሞት በኃላ በእውንነታቸው ቤተ ክርስቲያኒቱን  ወደ ቅድመ ግራኝ ክብሯና ልዕልናዋ  ይመልሷታል ተብለው ተስፋ  የተሰነቀባቸው የተቋማዊ ለውጥ  እንቕስቃሴዎች እና የፓትርያርክ ምርጫ ቀኖናዊነት  ከየት ተነስተው በምን መልኩ ተደመደሙ  ? የሚለው ነው፡፡        
  ከእነዘህ ሦስት መሠረታዊ ጥያቄዎች በመነሳት  ስንገመግምና አሁን እየሆነና እየተደረገ ባለው ሁኔታ የኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  ተቀጥፋ ያልደረቀች  አበባን መስላለች፡፡ያውም አጥር ቅጥር የሌላትን፡፡የሚቀጥፏት ወጪዎቹና ወራጆቹ ጆቢራዎቹ ብቻ ሳይሆኑ ወርቋን እንጂ የወርቁ መገኛ መሆኗን የዘነጉ ጳጳሳት መሆናቸው ደግሞ ነገሩን ግራ ያደርገዋል፡፡            
             ተቀጥፋ  እንዳትደርቅ  ተጨማሪ  አጥር ቅጥር ያበጃጁላታል ተብለው የተሾሙት  አበው ጳጳሳት አጥር ቅጥር መዝለላቸው ሳያንስ  ቀደምት አበው የሠሩትን  የእርቀ ሠላም ፣ዘመንን  የዋጀ ተቋማዊ  ለውጥና ሢመተ ፕትርክና  የሚመራበትን አጥር ቅጥር  አፍራሽ ኀይለ ግብር ሆነው ከመገለጣቸው በላይ ምን ግራ ያጋባል? ፡፡ 
ይህም ሆኖ አለመድረቋና በወርኃ ጽጌ እንደ አሉ አበባዎች ልምላሜ ሃይማኖትና መዐዛ ምግባር ከምዕመኑ አለመጥፋቱ እጅግ ይደንቃል፡፡ይህ የሆነው ግን    የሐዋርያት ውሳኔ በሆነው  በመጽሐፈ ዲድስቅልያለአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ኤጴስ ቆጶስ ሆኖ  የሚሾመውየምዕመናን ጠባቂ፣ነውረ የሌለበት፣ንጹሕና ቸር፤ የዚህንም ዓለም ጭንቀት የማያስብ ፣፶ ዓመት የሞላው፣ የጉልማሳነትኀይልን ያለፈ፣ ነገር  የማይሠራ፣ በወንድሞች መካከል ሐሰትን  የማይናገር  ይሆን ዘንድ  እንደ ሚገባው በጌታችን ኢየሱስክርስቶስ ዘንድ ሰማን፡፡በሚለው አምላከዊ ድንጋጌ መሠረት የተሾሙ ወይም ሆነው የተገኙ ጳጳሳት  ሰላሉን  አይደለም፡፡ጌታ ሰለ ቃልኪዳኑ ሰለሚጠብቃትና የቀደምት አበውና እመት በረከተ ጥላ ከለላ ሰለሚሆናት ብቻ ነው፡፡/ዲድስቅልያ4 1 /                                                                                                                         
           ቀድሞም አብዛኛቹ  በዚህ ውሳኔ  መሠረት ባለመሾማቸው እና በኃላም መለካውያን-ፈጻሚ ፈቃድ ቄሣር ሆነው መገኘታቸው  ጵጵስናቸውን አስኬማ  መላእክት አለመሆኑን ከማጋለጡም  በላይ አስኬማ ቄሣር አድርገን እንድንወስድ አድርጉናል ፡፡                                                                                                                                    
የቤተ ክህነቱ የችግር ሰኮፍ ከነአቶ ስብሐት ነጋ ቢመዘዝም  እዚህ ጋ ብቻ ከአቶ ስብሐት ነጋ  አሳብ ጋር እንድስማማ እገደዳለው፡፡ይኸውም  እነርሱ መጥተው ተጣበቁብን  እንጂ እኛ መች  ሔድንባቸውከሚለው  ጋር፡፡ የአብዛኛዎቹ  ጳጳሳት  የነገር ማንጸሪያ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሠረት እምነት፣ ሥርዐተ አምልኮ፣ቀኖናና ትውፊት ሳይሆን  ፈቃደ ቄሣር መሆኑ የአቶ ስብሐትን አሳብ ትክክል ያደርገዋል፡፡ሕገ ቤተ ክርስቲያን ምን ይላል? ከሚለው ይልቅ ቄሣራውያን ምን ይላሉ?የሚለው ቀልባቸውን በሚገዛ  ጳጳሳት በተወረረች ቤተ ክርስቲያን ሰለ እርቀ ሠላም፣ስለተቋማዊ  ለውጥና ሰለፓትርያርክ ምርጫ ውጤታማነት በራሱ ማሰብ አሰብኩ ፣አሰብኩናደከመኝ” እንዳለው ልጅ ነው ነገሩ ፡፡                                                                                                                                          

Wednesday 14 August 2013

ሠለስቱ ደቂቅን ያዳናቸው ማን ነው ?

ሰኮናቸው ያልተሰነጠቀና የማያመሰኩ እንስሳት (የዘመናችን ተሐድሶዎች)(የመጨረሻ ክፍል)
 
ታዲያ ሠለስቱ ደቂቅን ያወጣቸው ማን ነው?ለሚለው የተሐድሶዎች ጥያቄ የቀረበ መልስ 


መጀመሪውንም መጽሐፍ ቅዱሱ ገብርኤል ነው አይልም፡፡ መጽሐፍ ቅዱሱ የሚለው የሚከተለውን ነው፤ ‹‹ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ አማካሪዎቹንም፤ ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን? ብሎ ተናገራቸው። እነርሱም፦ ንጉሥ ሆይ፥ እውነት ነው ብለው ለንጉሡ መለሱለት። እርሱም፦ እነሆ፥ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል ብሎ መለሰ ›› /ዳን 3 ፤ 24 -25/ ፡፡ በዚህ ገለጻ መሠረት አራተኛውን ያየው ንጉሡ ናቡከደነጾር ነው፡፡ እርሱም አየሁ ያለው አራተኛ ሰው ነው፡፡ የጨመረበት ቢኖር አራተኛው የአማልክትን ልጅ ይመስላል የሚለውን ነው፡፡ ለመሆኑ አራተኛውን ሰው እርሱ ብቻ ለምን አየ ? ሌሎቹ ለምን አላዩም ? አንደኛው የጥያቄው ቁልፍ ምስጢር ያለው እዚህ ላይ ነው፡፡ እውነቱን ለመናገር ይህ ሰው ጥንቱንም ሠለስቱ ደቂቅን ወደ እሣት የጣለው ራሱን ምስል አቁሞ ለምስሉ ሕዝቡን በማሰገድ ራሱን አምላክ አድርጎ ሊያስመልክ ነበር፡፡ ታዲያ ራሱንና እርሱን የመሰሉትን አምላክ አድርጎ የሚቆጥር ከሆነ የሚያየውን አራተኛውን  ሰው ‹‹ የእኛን ልጅ ይመስላል ወይም እኛን ይመስላል›› ለምን አላለም? ከዚያ ይልቅ አርቆ ሌሎች አማልክትን የሚያመልክ አስመስሎ ‹‹ የአማልክትን ልጅ›› ይመስላል ያለበት ምስጢር ምንድን ነው ? ይህን ያለበት ምክንያቱ ያየው ነገር አራተኛው አካል ከህልውና ያለው በዘር በሩካቤ የተወለደ ሰው እነርሱ ሳያዩት እሳቱ ውስጥ ገብቶ ሳይሆን ነገሩ መገለጥ ስለሆነ ነው፡፡

ሰኮናቸው ያልተሰነጠቀና የማያመሰኩ እንስሳት (የዘመናችን ተሐድሶዎች)

ሠለስቱ ደቂቅን ያዳናቸው ማን ነው ለሚለው የተሐድሶዎች ጥያቄ የቀረበ መልስ

ሰሞኑን በተለይ በርከት ባሉት በመጽሐፈ ገጽ ወዳጆቼ በኩል  ‹‹ ሠለስቱ ደቂቅን ያዳናቸው ማን ነው? ›› የሚል ጥያቄ በተደጋጋሚ ቀርቦልኛል፡፡ በተሐድሶዎች በተሰራጨ አንድ የቪዲዮ ቁራጭ ላይ በሦስቱ ድርሳናት ማለትም በድርሳነ ገብርኤል ላይ ገብርኤል ፤ በድርሳነ ሚካኤል ላይ ሚካኤል ፤ በድርሳነ ራጉኤል ላይ ደግሞ ራጉኤል አዳናቸው ተብሎ ስለተገለጸ ትክክሉ የቱ ነው፤ በርግጥ ያዳናቸውስ ማን ነው የሚል ነው፡፡ በዚያም ጊዜ ሆነ ዛሬ ከአንዳንዶቹ መልእክት እንደተረዳሁት የድንጋጤ ስሜትም የተሰማቸው አሉ፡፡ ይህን ሌሎች ተመሳሳይ ድርጊቶችንም ስመለከት ለጉዳዩ ቢያንስ አንዲት ትንሽ መጣጥፍ እንዳአቅሜ  እንኳ ለጊዜው መስጠት እንዳለብኝ ስለተሰማኝ ጥያቄውን ለላካችሁልኝ ሁሉ ይህችን መቆያ እንካችሁ ብያለሁ፡፡ ዋናው ወይን ሁልጊዜም ወደ ኋላ መምጣቱ አይቀርምና እርሱን አብረን ከወይን አዳዩ እንጠብቃለን፡፡

Thursday 16 May 2013

የኤማሁስ መንገደኞች...ሉቃስ 24


በእታ ሰይፈ

ጸጥ ባለው አሸዋማ በረሃ ረጅሙን መንገድ ተያይዘውታል። ከመነሻቸው ጀምሮ እስከአሁን የመጡበትን ርቀት ባለማስተዋል
የልባቸውን ጭንቀት ያወጋሉ። ሰሞኑን በምድረ ኢየሩሳሌም ተደርጎ የማያውቅ ወደ ፊትም የማይደረግ ግፍ ተፈጽሟል፣ ፍርድ ተስተጓጉሏል። 

ሰዎቹ የጸሃዩን ግለት፣ የመንገዱን ርቀት፣ ረሃብና ድካሙን ረስተው ስለዚያ በግፍ ስለተገደለው ደግ ሰው ያወራሉ። አብሯቸው በቆየባቸው 3 አመታት ውስጥ ያዩትን የተለየ ፍቅር፣ ቸርነት፣ ትህትና፣ ደግነት፣ ተዓምራት እያሰቡ፡ ከአንደበቱ እንደ ማር እያዘነበ ያስተማራቸውን የጣፈጠ ቃል እያውጠነጠኑ ይነጋገራሉ። ፍቅሩ እንደ ልክፍት ተጠናውቷቸው ስለ እርሱ ከማሰ...ብ አልቦዘኑም። ስድሳውን ምዕራፍ እንደተጓዙ ያላስተዋሉት 3ኛ ሰው ተቀላቀላቸው። 

ድንገትም፦ 
"እንዲህ እየጠወለጋችሁ ስትሄዱ እርስ በርስ የምትነጋገሯቸው እነዚህ ነገሮች ምንድር ናቸው?"ሲል ጠየቃቸው። 
በንግግሩ እጅጉን ተገርመው ከሁለቱ አንዱ ቀለዮጳ ፈጠን በማለት፦ 
"አንተ ደግሞ በኢየሩሳሌም ስትኖር በእነዚህ ቀናት የሆነውን አታውቅምን?" አለው። ሰውየውም ምንም እንዳልሰማ በመሆን፦ 
"ይህ ነገር ምንድር ነው?" አላቸው። 
"ከወዴት ሀገር የመጣ እንግዳ ይሆን?" ሲሉ አሰቡና በእግዚአብሔርና በህዝቡ ፊት በቃልና በስራ ብርቱ ስለነበረው በግፍ ስለተሰቀለው ስለ ናዝሬቱ ኢየሱስ አንድ በአንድ አወሩለት። 

አስቀድሞ እንደሚነሳ ቢነግራቸውም አሁን ግን ሞቶ ከተቀበረ 3 ቀን ሆነው። በእስራኤል ሁሉ የሞቱ ወሬ ተናፍሶ እነርሱም ተስፋ ቆርጠው ወደ መንደራቸው ኤማሁስ እየተጓዙ ነው። ግን ደግሞ የዛሬው የሴቶቹ ወሬ አጠራጥሯቸዋል። ቀጠል አድርገውም አሁን ደግሞ ያስገረመን አሉ፦ 
"ከእኛ መካከል ማልደው ከመቃብሩ ዘንድ የሄዱ ሴቶች ስጋውን ባጡት ጊዜ ተነስቷል በዚያ የለም አሉን" 
አሉ ግራ በተጋባ በሰከነ ድምጽ። የልባቸውን መዛል የተመለከው በጸጥታ ታሪኩን ያዳምጥ የነበረው ሰው፦ 
" እናንተ የማታስተውሉ፥ነብያትም የተናገሩትንም ሁሉ ልባችሁ ከማመን የዘገየ፡ ክርስቶስ ይህን መከራ ይቀበል ዘንድና ወደ ክብሩ ይገባ ዘንድ ይገባው የለምን?"አላቸው። 
 ከሙሴና ከነብያት ጀምሮ ስለ እርሱ በመጽሃፍ የተነገረውን እየተረጎመላቸው ሳያስቡት ከመንደራቸው ደረሱ። ማንነቱን ያልተረዱት በቃሉ ብርታት የተማረኩት የሩቅ ተጓዥአብሯቸው ያድር ዘንድ ግድ አሉት። 
"ማታ ቀርቧልና፡ ቀኑም ሊመሽ ጀምሯልና እባክህ ከእና ጋር እደር?" አሉት በሚማጽን ንግግር።
 ሰውየው ቃላቸውን ተቀብሎ ከቤታቸው ገባና አብሯቸው በማዕድ ተቀመጠ። እንጀራንም በርኮ ሰጣቸው። ተከፍተው የማያዩ አይኖቻቸው ተከፈቱ፤ ሰውየውን አዩት፡ ያውቁታል። ረጅሙን መንገድ አብሯቸው የተጓዘው፣ንግግሩ ልባቸውን ያቀልጠው የነበረው፣ ከሞት የተነሳው እርሱ ኢየሱስ ነው። ሉቃስና ቀለዮጳ በደስታ ሰከሩ። ጊዜ ሳያባክኑ በፍጥነት ወደ ኢየሩሳሌም ሮጡ፤ ሁሉን በአንድ ቤት ውስጥ ተሰብስበው አገኛቸው።
"ተነስቷል! ተነስቷል! ጌታ በእውነት ተነስቷል" በደስታ ሲቃ ምስራቹን አበሰሯቸው።
 በመንገድ የተናገራቸውን፣ እንጀራም ሲሰጣቸው የሆነውን እየነገሯቸው ሳለ በብርሃን ጸዳል የተሞላ ድምጹ የሚያሳርፍ ሰው በመሃከላቸው ቆሞ 
"ሰላም ለእናንተ ይሁን" አላቸው፡፡ 
 በእርግጥ ኢየሱስ ነው። ምትሃት ያዩ መስሏቸው ፈሩ ደነገጡም፤ እርሱ ግን 
"እኔ ነኝ አትፍሩ አትደንግጡም፤ መንፈስ ስጋና ደም የለውም፡ እኔ እንደሆንኩ ታምኑ ዘንድ እጆቼንና እግሮቼን እዩ ዳስሱም" በማለት አረጋጋቸው።
 ኢየሱስን አዩት፥ ተነስቷል! ደስታቸው እጥፍ ሆኖ አይናቸውን ማመን ቸገራቸው። ልባቸውን ያወቀው አምላክ፡ እምነታቸው ሙሉ እንዳልሆነ ተመልክቶ 
"በዚህ አንዳች የሚበላ አላችሁን?" አላቸው።
 የተጠበሰ ዓሣ ቁራጭና የማር ወለላ አቀረቡለት፤ እምነታቸው ይሞላ ዘንድ ዛሬም እንደቀድሞው በመሃከላቸው ተመገበ። አብሯቸው ሳለ በሙሴ ህግና በመዝሙራት መጻህፍት መከራን እንዲቀበልና እንዲነሳ የተጻፈው ይፈጸም ዘንድ እንደሚገባው ያስተማራቸውን ያስታውሳቸው ጀመር... 

"ሰላም ለእናንተ ይሁን" ሉቃ 24:36...  
 እንኳን ለዳግማይ ትንሳኤ በሰላም 

አደረሳችሁ!!!..

Wednesday 3 April 2013

የአዲርቃይ ፍርድ ቤት ‹‹ዋልድባ አይታረስ›› ያሉትን ወጣቶች በአሸባሪነት ከሰሰ


  • አዲርቃይ ፍርድ ቤት ገዳማችን አይታረስም በማለታቸው ወጣቶችን በአሸባሪነት ከሰሰ
  • በዛሬማ የሚገኙ ነዋሪዎች በወጣቶቹ ላይ ምስክርነት አንሰጥም በማለታቸው እንግልትእየደረሰባቸው ነው
  • የሰሜን ጎንደር ጸጥታ ክፍል ክሱ በአሸባሪነት መሆን አለበት በማለት ትዕዛዝ አስተላልፏል
  • የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከገዳሙ በረከት ለመቀበል የመጡት ማስፈራሪያ እና ፍተሻ (strip search) ተደረገባቸው
  • የጣሊያኑ ኮንስትራክሽን ሌላ አማራጮችን እንፈልግ ብሏል
  • የወልቃይት ነዋሪም እርሻውን እንዲቀጥል እስከሚመጣው ዓመት ምንም ነገር እንደማይኖርእየተነገረው ነው

Thursday 28 March 2013

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት የመብት ጥያቄ በተሃድሶ መናፍቃን አጀንዳ ተጠለፈ



  • የደቀመዛሙርቱ አካዳሚክ፣ አስተዳደራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ወደ ግለሰቦች ኃላፊነት ማስነሳት በሚል ቅድመ ሁኔታ ተቀይሯል፡፡
  • “ተቃውሞውን አስተባብረሃል” በሚል ታስሮ የነበረው ደቀመዝሙር ከእስር ትናንት ተፈትቷል፡፡
  • የተሃድሶ ኑፋቄ አራማጅ የሆኑ ተማሪዎች ተቃውሞውን ኦርቶዶክሳውያንን ከኮሌጆ ቁልፍ ቦታ በማስወገድ በመናፍቃን ለመተካት በኅቡዕ እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡

(አንድ አድርገን መጋቢት 19 2005 ዓ.ም)፡- የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት በኮሌጁ ስላለው የአስተዳደር ጉድለት ፣ የትምህርት ጥራት ማነስና የምግብ አቅርቦት ጥራት መጓደል ተቃውሟቸውን በትምህርት ማቆምና የረሃብ አድማ በማድረግ እየገለጹ ነው፡፡ በርካታ መገፋት ቤተክህነቱ  እያደረሰባቸው የሚገኙት የነገረ መለኮት ምሩቃንና ደቀ መዛሙርት ያቀረቡት ተቃውሞ የቤተክህነቱን አስተዳደረዊና መንፈሳዊ ድቀት ርቀት እንደ ማሳያ ተደርጎ ተወስዶአል፡፡

፩ የቅዱሳን አባቶች ህይወት

ከዝክረ ቅዱሳን ዘተዋህዶ ቁ.፪
ትርጉም  በሃዜብ በርሄ

"እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንኩት እርሱንም እሻለሁ በህይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ እግዚአብሔርንም ደስ የሚያሰኘውን አይ ዘንድ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ።" መዝ 26:4

የቅድስና መሰረቱ ራስን መቆጣጠር መቻል፣የሚሰሩትንም ሆነ የሚናገሩትን ማስተዋልና ጠንቅቆ ማወቅ፣ ጎጂ ከሆኑ ልማዶች ራስን መቆጠብ፣ የሌሎችን ጉድለትና ስህተት ከማጉላት ይልቅ ፍቅረ እግዚአብሔርን እያሰቡ ከመልካም ምግባራቸው መማር መቻል፣ እኔ ከሁሉ ያነስኩ ነኝ ብሎ ማመንና ከምንም በላይ ደግሞ ከቤተ መቅደሱ አለመራቅ...ወዘተ ነው።ቅዱሳን አባቶች ፍቅራቸው ራስን አሳልፎ እስከመስጠት ነውና እውነተኛና ከቅን ልቡና የመነጨ ፍቅር መሆኑ አያጠያይቅም። ስለ ሃይማኖታቸው አንገታቸውን ለሰይፍ፣ ጀርባቸውን ለግርፋት፣ ፊታቸውን ለጽፋት ነፍሳቸውን ለሞት የሰጡና "ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ "ማቴ 5:6 የመጨረሻ ግባቸው የመንግስቱ ወራሾች መሆን ነው።

"ከዓለም ምንም አልፈልግም"


በአያሌው ዘኢየሱስ

ይህ ቃል አንድ ሰው የነፍሱን ነጻ መውጣት በሚሻበት ጊዜ ቅድሚያ ሰጥቶ ሊናገረው የሚገባው ቃል ነው።
ዓለም ያሏት ፈተናዎች ብቻ እንጂ ምንም የሚወደድ ነገር ስለሌላት ከእርሷ ምንም አልፈልግም።
ዓለም ለመስጠት በጣም ድሀ ስለሆነ ከእርሷ ምንም አልፈልግም። እኔ የምፈልገው ሁሉ በዓለም ካለ ዓለም ገነት ሆናለች ማለት ነው። በውስጧም ከቁሳዊ ነገሮች በስተቀር ምንም የለም። በእርግጥ እኔ የምፈልገው ሰማያዊ ነገሮችን ነው። ለመንፈሳዊ ህይወቴ እንዲጠቅመኝ።

Friday 15 March 2013

13 አክራሪዎች ከ27 መሳሪያ ጋር ተያዙ


(አንድ አድርገን መጋቢት 6 2005 ዓ.ም)፡-በተለያዩ ሃይማኖቶች ውስጥ ወይም በአንድ ሃይማኖት ውስጥ የሚገኙትን የተለያዩ  የእምነት ቡድኖች እንዲህ ናቸው ብሎ ለመሰየም የሚያስችል ገላጭና ተስማሚ ቃል ወይም ስያሜ መምረጥ ሁልጊዜም ቢሆን አስቸጋሪ ሥራ ነው፡፡ ቃሎቹ ገላጭ ናቸው ሲባል አልፎ አልፎ አንድ ላይ ፈራጅ ሆነውም ይገኛሉ፡፡ 

Tuesday 5 March 2013

ፍቅርና ሃይማኖት - ነፍስና ሥጋ በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ


(ምንጭ፡አዲስ ጉዳይ መጽሔት፣ ቅጽ 7፣ ቁጥር 153፣ የካቲት 2005)
 በአሁኑ ጊዜ ‹‹ፍቅር››ን የማይጠራው አለ ለማለት አይቻልም፡፡ አፍቃሪ -ተፈቃሪው፣ አጣይ-አፋቃሪው ፣ ሸምጋይ አስታራቂው፣ የሥነ ልቡና ባለሙያው፣ ጸሐፊ ደራሲው፣ አንባቢ ተርጓሚው፣ ሃይማኖት ሰባኪው፣ ልጅ አዋቂው፣ ከተሜ ገጠሬው ፣...ሁሉም ፍቅር ፍቅር ይላል፡፡ የሁሉም ፍቅር ግን አንድ ነው ለማለት የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ‹‹ አምላክ›› የሚለውን ቃል የምንጠቀመው ሁሉ ‹‹ አምላክ›› በምንለው አካል እንደምንለያየው ማለት ነው፡፡ ለምን ቀናሽ? ለምን ገደልህ? ለምን ከሳህ?ለምን ታመምሽ? ለምን ተጣላህ?... ለሚሉት ድኅረ ፈተና ወመከራ ጥያቄዎች ብዙ ጊዜ መልሳቸው ‹‹ ስለ ምወደው! ስለምወዳት!›› የሚለውነው፡፡ ይኸ የገረማቸውም እረ ለመሆኑ ‹‹ፍቅር›› ራሱ ምንድን ነው? ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡ በርግጥም ፍቅር ራሱ ምንድን ነው?

Tuesday 26 February 2013

የ5ቱ እጩ ፓትርያርኮች አጭር የሕይወት ታሪክ


PDF http://bit.ly/YwKqd1:- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 6ኛውን ፓትርያርክ ለመምረጥ በዝግጅት ላይ እንደምትገኝ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ አስመራጭ ኮሚቴ በመሠየም እጩ ፓትርያርኮችን ለመምረጥ ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት፤ ከካህናት፤ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች፤ ከማኅበረ ቅዱሳን፤ እንዲሁም ከምእመናን ጥቆማ እንዲያካሔዱ ተደርጓል፡፡ በተካሔደው ጥቆማ መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ጥቆማውን በግብአትነት በመጠቀም አምስት ሊቃነ ጳጳሳትን በእጩነት በማቅረብ የካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አቅርቧል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤም ከየካቲት 16 – 18 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ ውይይት በማካሔድ አምስቱም ሊቃነ ጳጳሳት በእጩነት እንዲቀርቡ አጽድቋል፡፡