የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ አስከሬን ሽኝት
ማውጫ፦ ዜና

- ግርግሩ መልክ ይያዝ::
- ሥርዐተ ቀብሩ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የቀጥታ ሥርጭት ይተላለፋል::
በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያው ሓላፊዎችና መላው ሠራተኞች፣ የየድርጅትና የየኮሌጁ ሓላፊዎችና ሠራተኞች፣ አገልጋዮችና ምእመናን ታጅቦ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ከገባ በኋላ በቅድስቱ ውስጥ ዐርፎ ጸሎተ ቅዳሴው በብፁዕ አቡነ ማቲያስ የካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መሪነት እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ከንጋቱ 12፡00 ላይ በመላው ኢትዮጵያ ገዳማትና አድባራት የደወል ድምፅ ተሰምቷል፡፡

በዛሬው የመርሐ ግብሩ ክንውን ሐዘንን ከመግለጽ ባሻገር በተለይም የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩን አስከሬን ይዞ ለማስገባት ከተመደቡት አባቶች ውጭ በአንዳንድ መነኰሳት ዘንድ የታየው ከፍተኛ ግርግር ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ነው፤ በቀጣይ የሥርዐተ ቀብሩ ሂደት ቢያንስ ከሚገኙት እንግዶችና በቴሌቪዥን ከሚሰጠው የቀጥታ ሥርጭት አንጻር ፈር መያዝና መስተካከል እንደሚገባው አስተያየት እየተሰጠበት ይገኛል፡፡

ቀሪውን የቀብር ሥነ ሥርዐት ክንውን ከመርሐ ግብሩ ይመልከቱ፡፡
የቅዱስነታቸውን ነፍስ በአብርሃም ዕቅፍ ያኑርልን
ቸር ወሬ ያሰማን፤
አሜን፡፡
No comments:
Post a Comment