Friday 31 August 2012


ቤተ ክርስቲያንና የፓትርያርክ ምርጫ (ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ)

ቤተ ክርስቲያን አንዲት፣ ቅድስት፣ ኩላዊትና ሐዋርያዊት መሆኗን ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያን ሁሉ ይቀበላሉ፤ በመሠረተ እምነታቸው ውስጥም አካትተው በጸሎትና በአስተምህሮ ይጠቀሙበታል፡፡የዚህ መሠረታዊ ምክንያቱ ደግሞ ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ ይህ ትምህርት ቢኖርም ነገር ግን መልእክቱን በአግባቡ ካለመረዳት የተነሣ እነ አርዮስና መቅዶንዮስ
በትውፊት ከሐዋርያት ጀምሮ የመጣውን የቅዱሳት መጻሕፍት ትርጓሜ መሠረት መቀበልን ቸል ብለው በራሳቸው መንገድ ሔደው ስለሳቱ በጉባኤ ኒቅያ በማያሻማ መንገድ ቤተ ክርስቲያን አንዲት፣ቅድስት፣ ሐዋርያዊት እና ኩላዊት መሆኗን አስቀመጡ፡፡ በኋላ በጉባኤ ቁስጥንጥንያ ደግሞ ሁላችንም እንድንጸልይበት በተዘጋጀው አንቀጸ ሃይማኖት ላይ (ጸሎተ ሃይማኖት) ‹‹ ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት›› የሚለው የጸሎታችን መፈጸሚያ እንዲሆን ተደነገገ፡፡ በዚህም መሠረት እነዚህን ዓለም አቀፍ ጉባኤያት የሚቀበሉ ሁሉ የሚቀበሉትና የሚመሩበት መሠረታዊ ትምህርተ ሃይማኖት /doctrine/ሆነ፡፡

‹‹የጎንደር ምንቸት ውጣ … የትግሬ ምንቸት ግባ›› በቤተ ክህነት (ነመራ ዋቀዮ ቶላ )

ይህ የቤተ ክክነታችን ችግር እውነታን የዳሰሰ ጡመራ የዛሬ አራት ዓመት አካባቢ ደጀ ሰላም ብሎግ አስነብባን ነበረ:: አሁንም በተለምዶ ስደተኛ ሲኖዶስ እየተባለ የሚጠራው ቡድን “መንበሩ ለእኔ ይገባኛል” እያለ ነው::ስደተኛው ሲኖዶስ የመሰረቱት በስደት ላይ ያሉት የጎንደር ተወላጅ የሆኑት ብፁዓን  አበው “በትግሬዎቹ/በወያኔ ተገፍተን መንበራችን ተቀማን” እያሉ ለ20 ዓመታት ያህል ምእመናን ሲያምሱ ኖረዋል:: በዚህም ምክንያት ቤተ ክርስቲያኒቷ በፍቅር መስፋፋት ሲገባት በውጩ ዓለም በጥላቻ እና በጎጠኝነት ለቁጥር በሚያስቸግር ሁኔታ ተከፋፍላለች:: እውነት የጎደሬዎቹ ወደ መንበር መምጣት የቤተ ክርስቲያኒቱ ችግር ይፈታ ይሆን??? አሐቲ ተዋሕዶ በአባቶች መካከል የተፈጠረው መከፋፈል አጥብቃ ትቃወማለች:: ጎጠኝነትን ግን ታወግዛለች::  በስደት ላይ የሚገኙት ብፁዓን አባቶች ከቅዱስ ሲኖዶስ ጋር ታርቀው ወደ አገራችው እንዲመለሱም እንፈልጋለን:: የአባቶች መታረቅ የሚመጣው ግን እውነታዎች ሳይደባበቁ በግልጽ አውጥተው ሲነጋገሩ ብቻ ነው ብላ አሐቲ ተዋሕዶ ታምናለች:: የሚከተለውን የነመራ ዋቀዮ ቶላ ጽሑፍ አንብቡት:: መልካም ንባብ::

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የተዘረጋባትን የተሐድሶ ወጥመድ ይፋ አድርጓል የተባለ “ሰነድ” ይፋ ሆነ

(ደጀ ሰላም፤ ፌብሩዋሪ 5/2011፤ ጥር 29/2003 ዓ.ም)፦ 

ከ1920ዎቹ ሁለተኛ አጋማሽ ጀምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ እና ትውፊት በመለወጥ ፕሮቴስታንታዊ ለማድረግ በተለያዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ አካላት እና መዋቅሮች ላይ ትኩረት ሰጥተው የሚሠሩ የተሐድሶ ኑፋቄ ማኅበራት እና ድርጅቶች በተለዋዋጭ ስልቶች ሲማስኑ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡ ይህ ጥረታቸው ያሰቡትን ያህል ያልተራመደላቸው የተሐድሶ መናፍቃኑ ቤተ ክርስቲያኒቱን ‹‹ከውስጥ እያጠቁ ወደ ውጭ በመገስገስ እና ከውጭ ከበባውን አጠናክሮ ወደ ውስጥ በመግፋት›› ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር አልያም ውጥንቅጧን አውጥቶ ለሁለት ለመክፈል ስልት ቀይሰው፣ በተለይም የቤተ ክርስቲያኒቱን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማእከል አድርገው በመንቀሳቀስ ላይ ስለመሆናቸው የሚገልጽ ሰነድ ሰሞኑን ለደጀ ሰላም ደርሷል፡፡

Thursday 30 August 2012


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ የት ነዎት?


  •  ቅዱስነታቸው ስለ ራሳቸው እና ስለ ፕትርክናው ሊናገሩ ይገባቸዋል።

(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 25/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 31/ 2012/READ THIS ARTICLE IN PDF)፦  ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስአርፈው መንበረ ፕትርክናው ባዶ ከሆነ እነሆ ቀናት ተቆጠሩ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ባለው ሥልጣን መሠረት ተተኪው ፓትርያርክ እስከሚሰየም ድረስ አቃቤ መንበረ ፓትርያርክ” ይሆኑ ዘንድ ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን ሰይሟል። ቤተ ክርስቲያኒቱ 5ኛውን ፓትርያርኳን በሐዘን እያሰበች ባለችበት በአሁኑ ወቅት “ቀጣዩ ማን ነው?” የሚለው ጥያቄ በስፋት በመጠየቅ ላይ ይገኛል። ድምጻቸው ቀላል ያልሆኑ ኦርቶዶክሳውያንም “እግዚአብሔር ለቤተ ክርስቲያኒቱ አንድነት ሊሰጥ ዕድል ከፍቶልን ሳለ፣ የቀደሙትን አራተኛውን ፓትርያርክ ወደ መንበራቸው መመለስ ሲገባ የምን አዲስ ምርጫ ነው?” እያሉ ነው። ለደጀ ሰላም የደረሱ ብዙ መልእክቶችም ይህንን በማበከር ላይ ይገኛሉ። በዚህ አጋጣሚ ደጀ ሰላም” አንድ ሁነኛ ጥያቄ ማቅረብ ትፈልጋለች። የቀድሞው ፓትርያርክ አቡነ መርቆርዮስ የት ነዎት? ድምጽዎትን ለምን አንሰማም? ሐሳብዎን ለምን አይገልጹም? ከምዕመኖችዎ ጋር በቱርጁማን፣ በስማ በለው፣ በተላላኪ፣ በሦስተኛ ወገን መነጋገር መቼ ነው የሚያበቃው ለማለት እንወዳለን። አንባብያንም ሐሳባችሁን እንድታካፍሉን እንጋብዛለን።
ቸር ወሬ ያሰማን፤
አሜን፡፡

ዮሐንስ ሐፂር


ዱስ ዮሐንስ ሐፂር በዲ/ን መላኩ እዘዘው
ዮሐንስ ሐፂር በላይኛው ግብጽ ቴባን በምትባል መንደር በ339 ዓ.ም ተወለደ፡፡ ወደ ገዳም አስቄጥስ የገባው በልጅነቱ ሲሆን ያን ጊዜ አበምኔቱ አባ ባሞይ ይባል ነበር፡፡ አባ ዮሐንስ በተመሥጦው እና በታዛዥነቱ የታወቀ አባት ነበር፡፡ በመጀመርያው የአስቄጥስ ጥፋት ጊዜ ገዳሙን ትቶ ወደ ቁልዝም ተጓዘ፡፡ ያረፈውም በዚያ ነው፡፡
የዮሐንስ ሐጺርን ትምህርቶች ከዚህ እንደሚከተለው አቅርበነዋል ፡፡
1. የጠላቱን ከተማ ለመቆጣጠር የዘመተ ንጉሥ አስቀድሞ የውኃውን መንገድ ይዘጋል፣ የእህሉንም መግቢያ ይይዛል፡፡ ያን ጊዜ ጠላቶቹ ይራባሉ፣ ይጠማሉ፡፡ በመጨረሻም እጃቸውን ይሰጣሉ፡፡ የነፍስን ፆር ለማሸነፍም በተመሳሳይ መንገድ መጠቀም ይገባል፡፡ አንድ ሰው በጾምና በረኃብ ከጸና የነፍሱ ጠላቶች ይዳከማሉ፡፡
2. እኔ በትልቅ ዋርካ ሥር የተቀመጠንና አራዊት ሊጣሉት የመጣን ሰው እመስላለሁ፡፡ ሊቋቋማቸው እንደማይችል ከተረዳ ሸሽቶ ወደ ዛፉ በመውጣት ነፍሱን ያድናል፡፡ በእኔም የተፈጸመው ይኼው ነው፡፡ በበዓቴ ተቀምጬ ክፉ ሃሳቦች ሊቃወሙኝ ሲመጡ፣ ልቋቋማቸው እንደማልችል ባወቅኩ ጊዜ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ሸሽቼ እመሽጋለሁ፡፡ በዚያም ከጠላቶቼ ፍላፃ እድናለሁ፡፡ 

3. መለወጥ የምትፈልግን ነፍስ በተመለከተ አባ ዮሐንስ እንዲህ አለ፡- በአንዲት ከተማ ውስጥ ብዙ ወዳጆች የነበሯት አንዲት አመንዝራ ሴት ነበረች፡፡ ከገዥዎቹ አንዱ ቀረባትና ‹መልካም ሴት ለመሆን ቃል ግቢልኝና አገባሻለሁ› አላት፡፡ እርሷም ቃል ገባችለትና ተጋቡ፡፡ ወደ ቤቱም ወሰዳት፡፡ የቀድሞ አፍቃሪዎቿ ያቺን ሴት ፈለጓት፣ እርስ በርሳቸውም ‹ያ ልዑል ወደ ቤቱ ወስዷታል፤ ወደ ቤቱ ብንሄድ ይቀጣናል፡፡ ነገር ግን በጓሮ በኩል እንሂድ፣ ለርሷም እናፏጭላት፣ የፉጨቱን ድምፅ ስትሰማ ከድርሱ ወርዳ ወደኛ ትመጣለች፣በዚህም ያለ ችግር እናገኛታለን› ተባባሉ፡፡ ወደ ቤቷም ጓሮ ተጉዘው ያፏጩ ጀመር፡፡ እርሷ ግን የፉጨቱን ድምፅ ስትሰማ ጆሮዎቿን ደፈነች፡፡ ወደ ውስጣዊው እልፍኝም ገባች፡፡ በሩንም ጥርቅም አድርጋ ዘጋች፡፡ ይህቺ ሴት የኛ ነፍስ ምሳሌ ናት፡፡ ወዳጆቿ የተባሉም ፈተናዎቿ ናቸው፤ ገዥ የተባለውም ክርስቶስ ነው፣ እልፍኝ የተባለውም ዘለዓለማዊው ቤት ነው፡፡ እነዚያ የሚያፏጩት ክፉዎች አጋንንት ናቸው፤ ነገር ግን ነፍስ ሁልጊዝም በክርስቶስ አምባነት ትሸሸጋዋለች፡፡

4. አባ ዮሐንስ ልቡናው ከእግዚአብሔር ጋር ስለነበረ ምድራዊ ነገሮችን ይዘነጋ ነበር፡፡ አንድ ቀን አንድ ወንድም ቅርጫት ሊወስድ ወደ አባ ዮሐንስ በኣት መጣ፡፡ አባ ዮሐንስም ምን ፈልጐ እንደሆነ ጠየቀው፡፡ ያም ወንድም ‹ቅርጫት ፈልጌ ነው› አለው፡፡ አባ ዮሐንስ ወደ በኣቱ ተመለሰና ዘንግቶት ወደ ሽመና ሥራው አመራ፡፡ ጥቂት ቆይቶ ያ ወንድም አንኳኳ፣ አባ ዮሐንስም ወጥቶ ‹ምን ፈልገህ ነው› አለው ‹ቅርጫት ስጠኝ ብየህ ነበር› ሲል መለሰለት፡፡ ተመልሶ ወደ በኣቱ ሲገባ ልቡናው በሰማያዊ ነገር ስለተመሰጠ ዘንግቶት ወደ ሽመናው ሥራ እንደገና ገባ፡፡ ለሦስተኛ ጊዜ ያ ወንድም ሲያንኳኳ አባ ዮሐንስ ተመልሶ ወጣና ‹ምን ፈልገህ ነው?› አለው፡፡ ‹ቅርጫት ስጠኝ ብየህ ነበር› አለና መለሰለት፡፡ አባ ዮሐንስም እጁን ይዞ እየጐተተ ወደ በኣቱ አስገባውና ‹ቅርጫት ከፈለግህ ያዝና ሂድ፣ በእውነቱ እንዲህ ላሉት ነገሮች እኔ ጊዜ የለኝም› አለው፡፡

5. አንድ ቀን አንድ ሰው ወደ አባ ዮሐንስ ሐፂር በኣት መጣና ሥራውን እያየ ያመሰግነው ጀምር፡፡ አባ ዮሐንስ ዝም አለውና ገመድ መሥራቱን ቀጠለ፡፡ እንግዳውም እንደገና ወሬውን ቀጠለ፣ አባ ዮሐንስም ጸጥ አለው፡፡ ለሦስተኛ ጊዜ እንግዳው ወሬ ሲያበዛ፡፡ ‹አንተ ወደ በኣቴ በመግባትህ እግዚአብሔር ወጥቶ ሄደ› ብሎ ተናገረው፡፡

6. አባ ዮሐንስ እንዲህ አለ፡- ‹የብሕትውናን ኑሮ በከተማ ውስጥ የሚኖር አንድ ሽማግሌ ነበረ፡፡ ያ ሰው በከተማው ውስጥ ከፍተኛ ቦታ የሚሰጠውና ባለዝናም ነበር፡፡ አንድ አረጋዊ አባት ከማረፉ በፊት ያንን ሰው ሊያየው እንደሚፈልግ ለዚያ ሰው ጥሪ ደረሰው፡፡ ያም ሰው በቀን ከተጓዝኩ ሰዎች ስለሚከተሉኝ ለኔ የተለየ ክብር ይሰጡኛል ብሎ አሰበ፡፡ ስለዚህም በሌሊት ሰው ሳያየው ለመጓዝ ወሰነ፡፡ በመሸ ጊዜም አሁን ማንም አያየኝም ብሎ ተነሣና ጉዞ ጀመረ፡፡ ነገር ግን ሁለት መላእክት ታዝዘው መብራተ ይዘው መንገዱን ይመሩት ነበር፡፡ ይህንን የተመለከቱ የከተማው ሰዎች ወደ እርሱ ተሰባሰቡ፣ መላ ከተማው ያንን የመላእክት ብርሃን እያየ ከኋላ ተከተለው፡፡ ከክብር በሸሸ ቁጥር የበለጠ ክብርን አገኘ፡፡ በዚህም ‹ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፣ ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ከፍ ይላል› የሚለው የወንጌል ቃል ተፈጸመ፡፡ (ሉቃ. 14.11)

7. አባ ጴሜን አባ ዮሐንስ እንዲህ ብሎ መናገሩን ገልጧል ‹ቅዱሳን በአንድ ቦታ የበቀሉ ዛፎችን ይመስላሉ፡፡ ከአንድ ምንጭ ጠጥተው፣ ልዩ ልዩ ዓይነት ፍሬ ያፈራሉ፡፡ የአንድ ቅዱስ ሥራ ከሌላው ይለያል፣ ነገር ግን በሁሉም አድሮ የሚሠራው አንድ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
ዋቢ መጽሐፍ በበረሓው ጉያ ውስጥ
በረከተ ቅዱሳን ይደርብን

Monday 27 August 2012


የዋልድባ አብረንታንት መነኰሳት መሰደድ ጀምረዋል


  • ባለፉት ጥቂት ቀናት ከስድስት ያላነሱ መነኰሳት ተሰደዋል
  • “ታጋይ ገድላችኹ እናንተ አትኖሩም” (የፀለምት - ማይ ፀብሪ ወረዳ ሓላፊዎች)።

 (ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 21/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 27/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦ በዋልድባ አብረንታንት ገዳም መነኰሳት ላይ ባተኰረውና ካለፉት አራት ቀናት ጀምሮ እየተባባሰ በቀጠለው እስርና እንግልት ሳቢያ ከስድስት ያላነሱ መነኰሳት የፀለምት - ማይ ፀብሪ የፀጥታ ኀይሎች በሚያደርሱባቸው ግፍ ሳቢያ ወደ ሌሎች ገዳማት መሰደዳቸውን፣ በተቀሩትም አባቶች ላይ ድብደባ እየተፈጸመባቸው መኾኑን የሥፍራው ምንጮች እየገለጹ ናቸው፡፡


Wednesday 22 August 2012

Tewodros Yosef Mariam mariam biye

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ፓሮቴስታንታዊ መሪ አስተናገደች

ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት መቼም የማይነጣጠሉ ነበር ዛሬ ዛሬ ግን ቤተ ክርስቲያናችን ተሰሚነቷ እየቀነስ አመራሩ አካል ጫና እያሳደረባት እና ቤተ ክርስቲያኗ እንኳን ሲቃጠሉ ሀይ ባይ እያጣች መጥቶ ዛሬ ደግሞ ይህ አልበቃ ብሎ ኢትዮጵያ እና ኦርቶዶክስ ተፋተው የፕሮቴስታንት ሃይማኖት ተከታይ መሪ ለማስተናገድ በቃች፡፡

መቼም ሁላችሁም እንደምትገምቱት ሐይለማርያም ብሎ ፓሮቴስታንት አይኖርም አይደረግም ብላችሁ ተገምቱ ይሆናል ነገር ግን በደቡቡ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንሰራፍ ያለው የፕሮቴስታንት እምነት ወደድንም ጠላንም አሁን መሪ የተባሉትን ጠቅላይ ሚንስቴር ሀይለ ማርያም ደሳለኝን ሳይቀር  ሰለባ አድርጓቸዋል፡፡ ወላይታና አካባቢውም ቢሆን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ተኩረት ባለመስጠቷ ብዙዎቹ ካደጉባት ቤተ ክርስቲያን   አስተምህሮዋን ባለመረዳት ኮብልለዋል፡፡ እግዚአብሔር ወደ እናት ቤታቸው እስኪመልስልን ልንፀልይ ይገባልእኛ የምንሰራቸው የቤተ ክርስቲያናችን ስራዎች ግን በዝተዋል ፡፡


የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ አስከሬን ሽኝት


  • ግርግሩ መልክ ይያዝ::
  • ሥርዐተ ቀብሩ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የቀጥታ ሥርጭት ይተላለፋል::
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 16/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 22/ 2012/READ THIS NEWS IN PDF)፦  የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አስከሬን፣ ተጠብቆ ከቆየበት ሃያት ሆስፒታል ዛሬ፣ ነሐሴ 16 ቀን 2004 ዓ.ም፣ 5፡00 ላይ ወደ መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ደርሷል፡፡

በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያው ሓላፊዎችና መላው ሠራተኞች፣ የየድርጅትና የየኮሌጁ ሓላፊዎችና ሠራተኞች፣ አገልጋዮችና ምእመናን ታጅቦ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ከገባ በኋላ በቅድስቱ ውስጥ ዐርፎ ጸሎተ ቅዳሴው በብፁዕ አቡነ ማቲያስ የካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መሪነት እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ከንጋቱ 12፡00 ላይ በመላው ኢትዮጵያ ገዳማትና አድባራት የደወል ድምፅ ተሰምቷል፡፡

በወጣው መርሐ ግብር መሠረት የቅዳሴው ሥነ ሥርዐት እንዳበቃ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ አስከሬን በልዩ ሠረገላ ኾኖ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ በሚኒስትሮችና የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ በገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ በሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፣ በፖሊስ ሠራዊት ባንድ፣ በምእመናንና ምእመናት ታጅቦ ወደ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጉዞ ያደርጋል፡፡ በዚህ ጉዞ የፖሊስ ሠራዊት ግራና ቀኝ በሰልፍ አስከሬኑን ያጅባል፡፡ የቅዱስነታቸው አስከሬን በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንዳረፈ የዕለቱ መርሐ ግብር በጸሎት ይዘጋል፡፡ ረቡዕ ለኀሙስ አጥቢያ ከምሽቱ 2፡00 እስከ ንጋቱ 12፡00 ሙሉ ጸሎተ ማሕሌቱ ሲከናወን ያድራል፡፡

በዛሬው የመርሐ ግብሩ ክንውን ሐዘንን ከመግለጽ ባሻገር በተለይም የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩን አስከሬን ይዞ ለማስገባት ከተመደቡት አባቶች ውጭ በአንዳንድ መነኰሳት ዘንድ የታየው ከፍተኛ ግርግር ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ነው፤ በቀጣይ የሥርዐተ ቀብሩ ሂደት ቢያንስ ከሚገኙት እንግዶችና በቴሌቪዥን ከሚሰጠው የቀጥታ ሥርጭት አንጻር ፈር መያዝና መስተካከል እንደሚገባው አስተያየት እየተሰጠበት ይገኛል፡፡

እስከ አሁን በሥነ ሥርዐቱ ላይ የቅብጥ፣ የሶርያ፣ የአርመንና ሕንድ /ማላባር/ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያን ልኡካን እንዲሁም የግሪክ ኦርቶዶክስ ተወካዮችና የመሳሰሉት እንግዶች እንደሚገኙ ማረጋገጣቸው ተገልጧል፡፡
ቀሪውን የቀብር ሥነ ሥርዐት ክንውን ከመርሐ ግብሩ ይመልከቱ፡፡

የቅዱስነታቸውን ነፍስ በአብርሃም ዕቅፍ ያኑርልን
ቸር ወሬ ያሰማን፤
አሜን፡፡


የአቡነ ጳውሎስ የቀብር ስርዓት እና የመለስ ዜናዊ አስከሬን አቀባበል



  • የአቶ መለስ ዜናዊ አስከሬናቸው ቢያንስ ለአንድ ሳምንት በብሔራዊ ቤተመንግስት ይቆያል ፤ ህዝቡም በቦታው በመገኝት ይሰናበታቸዋል ተብሎ ይጠበቃል

(አንድ አድርገን ነሐሴ 16 ፤ 2004 ዓ.ም) ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አስከሬን ከባልቻ ሆስፒታው ወደ ሐያት ጠቅላላ ሆስፒታል መሸጋገሩ ይታወቃል ፤ ቀድሞ የታሰበው ብጹእነታቸው አስከሬን ረቡዕ ከሰዓት ወደ መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ከተወሰደ በኋላ ጸሎት ተደርጎለት ከመንበረ ፓትርያርክ ወጥቶ ወደ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስትያን በሰረገላ በመውሰድ ለሊቱን ሙሉ ጸሎት በማድረግ ጠዋት ቅዳሴ በማድረግ ከጠዋቱ 4 ሰዓት ግድም ወደ ውጭ አውጥቶ ስርዓቱን ለማከናወን ታስቦ ነበር ፤ ነገር ግን አሁን በደረሰን መረጃ የብጹእነታቸው አስከሬን ዛሬ ጠዋት 3 ሰዓት ከሐያት ሆስፒታል ወደ መንበረ ፓትርያርክ በመውሰድ የከሰዓት በኋላ ቅዳሴውን በማድረግ አመሻሹ ላይ ወደ ቅድስት ስላሴ እንደሚሄድ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በነገው እለት የቀብር ስነስርዓታቸው እንደሚፈጸም ይታወቃል ፤ 


ከዚህ ጋር በተያያዘ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ድንገተኛ  ሞት ብዙዎችን አሳዝኗል ፤አቶ መለስ ግንቦት ልደታ 1947 ዓ.ም እንደተወለዱ የህይወት ታሪካቸው ይናገራል ፤ በ57 ዓመታቸው  ነሐሴ 15 2004 ዓ.ም ቀን የሱባኤው ቀናት ሊጠናቀቅ አንድ ቀን ሲቀረው ከዚህ ዓለም በህይወት ተለይተዋል ፤ በትላንትናው እለት ማታ 4 ሰዓት አስከሬናቸው ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ በደረሰበት ጊዜ የመንግስት ባለስልጣናት ፤ ቤተሰቦቻቸው ፤ ከየክፍለ ከተማው በቅጥቅጥ አይሱዙ ተጭነው የመጡ ሰዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል ፤ አስከሬናቸው አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ በመልበስ ከአውሮፕላን ወርዷል ፤ ኢትዮጵያ ቴሊቪዥን በቦሌ አለም ዓቀፍ አየር ማረፊያ እና በቦሌ መድኃኔአለም ቤተክርስትያን ጊዜያዊ ስቱዲዮ በማዘጋጀት ስርዓቱን በቀጥታ ማተላለፍ ችሏል ፤ 

ስርዓቱን ግማሹን በቴሌቪዥንም  ቀሪውን በአካልም ስርዓቱን መታደም ችለን ነበር ፤ አስከሬናቸውን የክብር ልብስ በለበሱ 8 አባላት በማስሳ ወደተዘጋጀለት ቦታ ማስቀመጥ ችለዋል ፤ ዘወትር እጃቸውን ወደ ላይ በማንሳት ከውሮፕላን ሲወርዱ የምናቃቸው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዛሬ እለተ ቀናቸው ደርሶ ፤ የእግዚአብሔር ጥሪ ሆኖ በሳጥን አስከሬናቸው ከአውሮፕላን ላይ ወርዷል ፤ ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው ይመስለናል ፤ ህዝቡ መሪ አስታሞም ሆነ መሪ ሲሞት ቀብሮ አያውቅም ፤ ቴዎድሮስ ለጠላት እጅ ላለመስጠት ራሳቸውን በአንዲት ጥይት አጠፉ ፤ አጼ ዮሀንስ በደርቡሽ ተገደሉ ፤ እምዬ ሚኒሊክ አስከሬናቸው 4 ዓመት ሀገሪቱን ገዛ ፤ ይህ የሆነው ሀገሪቱ ውስጥ ችግር ይፈጠራል በማለት ነበር ፤ አጼ ኃይለስላሴ በደርግ አመራሮች በትራስ ታፍነው እዛው ቤተመንግስት ተቀብረው ከዘመናት በኋላ ሬሳቸው በማውጣት ቅድስት ስላሴ ቤተክርስትያን እንዲያርፉ ተደረጉ ፤ ጓድ መንግስቱ ኃይለማርያር የዚችን ሀገር መጨረሻ አሳየኝ ብሎ የጸለየ ይመስል ከስልጣን ከወረደ በኋላ ይህው 21 ዓመት በዚምባብዌ ሰላማዊ ህይወቱን እያሳለፈ ይገኛል ፤ አራት ኪሎ ቤተመንግስቱን ለአቶ መለስ ቦታውን ለቆ እሱ በህይወት እያለ የእሳቸው ሞት ቀደመ ፤ ስለዚህ አሁን ላይ አቶ መለስ ዜናው ስልጣኑን እንደያዙ ከአሁን አሁን ስልጣኔን አስረክባለሁ እያሉ መልአከ ሞት ቀድማቸው ፤ ህዝባችን መሪ ሞቶ ቀብሮ አያውቅም ፤ ኢቲቪም መሪ ሞቶ ምን አይነት የሀዘን ካሴቶችን መክፈት ስለማያውቅ ትላንትና እስከ 2 ሰዓት ድረስ በፒያኖ በጃዝ እና በጊታር የተሰራ የቆዩ ክላሲካሎችን ሲያስተላልፍ ቆይቷል ፡፡


የአቶ መለስ ዜናዊ አስከሬን በመከላከያ ባንድ አቀባበል ከተደረገለት በኋላ ጥቁር መኪና አረንጓዴ ቢጫ ቀይ የለበሰች መኪና ውስጥ ተከቷል ፤ ለዚች ሀገር ለዛውም በአሁኑ ሰዓት መሪ ማጣት እጅጉን ያሳዝናል ፤ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች “እንወድሀለን” ፤ “እናከብርሀለን” ፤ “ታላቁ መሪያችን” ፤ “አባይ ይገደባል መለስ ይታወሳል” ፤ “አፍሪካ ታላቅ መሪዋን አጣች” የሚል መፈክር ይዘው በመንገድ ዳር ታይተዋል ፤ ዝናቡን በመቻል ሳይታክቱ ከ1 ሰዓት አንስተው አስከ 5 ሰዓት ድረስ አስከሬኑን ጠብቀውታል ፤ ከከተማዋ መብራቶች በተጨማሪ ብዙዎች ጧፍ በማብራት ተስተውለዋል ፤ የጧፍ ሽያጭ ባልታሰበ ሰዓት እጅጉን ደርቷል ፤ አንዳንድ ሰዎችም አስከሬኑ እስኪመጣ የእንግሊዝን ፕሪምየር ሊግ የሚቃኙ አልጠፉም ፤ በቅርቡ ከአርሰናል ወደ ማንችስተር ስለተዘዋወረው ተጨዋች የደራ ክርክርም ይዘው ነበር ፤ ኡራኤል አካባቢ ያለው ሰው በማታ እጅግ ብዙ ነበር ፤ ፌደራል ፖሊስ ከቦሌ አንስቶ እስከ መድረሻው ብሔራዊ ቤተመንግስት ድረስ እጅጉን በዝተው ሰላም የማስጠበቅ ስራ ላይ ተሰማርተዋል ፤ ወደፊት እጣ ክፍሉ ያልታወቀው በቦሌ መድኃኒዓለም ቤተክርስትያን የቆመውን የአቡነ ጳውሎስን ሀውልት ደግሞ ደጋግሞ ቴሌቪዥን ስክሪን ላይ ተመልክተናል፡፡


በቴሌቪዥን አንዲት እናት “ለማነው አደራው?” እያሉ ሲያለቅሱ ተስተውለዋል ፤ ትክክል ናቸው አደራ የሚቀበል ሰው ያስፈልጋል ፤ እኛ ለምዶብን ቅብብሎሽ ስላለመድን እኛው ጀምረን እኛው ሁሉን የምንጨርስ ይመስለናል ፤ ነገር ግን ሀገርን በቅብብሎሽ ነው የተሻለ ደረጃ ላይ ማድረስ የምንችለው ፤ አባቶቻችን ሀገሪቷን ነጻነቷን አስጠብቀው ለእኛ አስረክበውናል ፤ እኛም የራሳችንን ስራ በመስራት ለልጆቻችን ማስተላለፍ ነው ስራችን ፤ በእኛ ዘመን ጀማሪ እንጂ ፈጻሚ አለመሆናችንን ማወቅ መቻል አለብን ፤  የሀገራችን መሪዎች ትልቁ ችግራቸው መሪ ማፍራት አልፈጠረባቸውም ፤ ወንበሩ ዘላለማዊ ይመስል ሞታቸውን አስበው በተመረጡበት ጊዜያት አያገለግሉም ፤ አሁን ህዝቡን ያሳሰበው ነገር ከጠቅላይ ሚኒስቴር ሞት በተጨማሪ የእሳቸውን ቦታ ማን ሊይዝ ይችላል? የሚለው ጥያቄ ነው ፤ በ21 ዓመታት ከእሳቸው ጎን ለጎን የሚሰሩትን ተመልክቶ የሚተካቸው ሰው አልተመለከትንም ፤ በመሰረቱ መሪ እና ስልጣን የሚሰጥ እግዚአብሔር ነው ፤ አሁንም ለሐገራችን ጥሩ አመለካከት ያለው ፤ ጎጠኝነት ያላጠቃው ፤ ዘረኝነት ያልደረሰበት ፤ የተማረና በእውቀት የዘመነ ፤ ከግለሰብ አንስቶ የህዝብን መብት የሚያስጠብቅ ፤ ህዝብን የሚያከብር ፤ እግዚአብሔርን የሚፈራ ፤ ሞቱን አስቦ የሚያገለግል ፤ አሁን ያለውን ጭላንጭል ወደ ትልቅ ብርሐን የሚለውጥ አስተዋይና ቅን መሪ ይስጠን እንላለን ፤ በተለይ ለቤተክርስትያናችን ደግሞ  በእግዚአብሔር የተመረጠ ፓትርያርክ ያድላት ፡፡ 


ሥልጣን ከሰማያት እንደ ሆነ ካወቅህ በኋላ መንግሥትህ ይቆይልሃል።”ትንቢተ ዳንኤል 4፤26በአሁኑ ሰዓት በተለያየ የቤተክርስትያን እና የመንግስት የስልጣን ቦታ ላይ የምትገኙ ሰዎች የያዛችሁትን ስልጣን ከላይ እንደሆነ አውቃችሁ እና አምናችሁ በቅን ልቦና ልታገለግሉ ይገባችኋል ፤ በራሳችን መንገድ ተንጠላጥለን ያለ እግዚአብሔር መልካም ፍቃድ የምንቀመጥበት ስልጣን የለም ፤ በተቻለን መጠን ለራሳችን ለእምነታችን ለተሰጠን ኃላፊነት ቦታ ታማኝ ሆነን ማገልገል መቻል አለብን ፤ “ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና፤” ወደ ሮሜ ሰዎች 13፤1 ስልጣን የሚሰጥ እግዚአብሔር ነው ፤ የሚነሳም እሱ ነው ፤ እርሱ ከእርሱ ካልሆነ ስልጣን የለም ፤ የሰለሞንም የዘውድ ስርዓት አልፏል ፤ ሞት ትምህርት ሊሆነን ይገባል ፤ ሰው ነን እንወለዳለን እንኖራለን በመጨረሻም እንሞታለን ፤ ይህን አስበን በንስሀ ህይወት እየተመላለስን ልንኖር ያስፈልጋል ፤ 2004 ዓ.ም ኢትዮጵያ ታላላቅ ጸሀፍትን ፤ አለማቀፋዊ እውቅና ያለው ሰዓሊን ፤ የኦርቶዶክስ ተዋህዶን ፓትርያርክ ፤ አሁን ደግሞ የሀገሪቱን ስመ ጥር መሪ መለስ ዜናዊን ያጣችበት ዘመን ነው ፤ አሁንም እግዚአብሔር በቃችሁ እንዲለን ልንጸልይ ያስፈልጋል ፤ ቤተክርስትያን ስለ ሀገር ሰላም እንድትሆን ፤  መሪዎችን ማስተዋልና ጥበብን እንዲሰጣቸው ፤ ስለ ህዝበ ክርስትያን  ፤ ዘወትር በቅዳሴ ላይ ጸሎት ታደርጋለች ፤ እኛም እስኪ ሱባኤው በእንዲህ አይነት ሁኔታ አልፏል ፤ ቀሪዎቹን የአዲስ ዘመን መቀበያ ቀናት ሌላ እንዳይጨምርብን ተግተን እንጸልይ ፤   

ስለ ቤተክርስቲያን ጸልዩ
ስለ ሀገር ሰላም ጸልዩ
ስለ ህዝበ ክርስቲያን ጸልዩ
ለሁላችን እግዚአብሔር መጽናናቱን ይስጠን

የአቡነ ጳውሎስ አስከሬን እንደ አቡነ ሺኖዳ በመስታወት ሬሳ ሳጥን ቤተክህነት ደርሷል


ከአንድ አድርገን ድህረ ገጽ ላይ የተወሰደ
Photographer:- LAMBDA



























አቡነ ዮሀንስ ከዚሀ ዓለም በሞት ተለዩ ፤



አቡነ ዮሀንስ የከሳቴ ብርሀን መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ መሆናቸው ይታወቃል
  • ስለ ቤተክርስትያን ጸልዩ
  • ስለ ህዝበ ክርስትያን ጸልዩ
  • ስለ ሀገር ሰለም ጸልዩ

አሁንስ ፈራን!!! 


ይህን ጊዜ ያሳልፍልን ፤ ይህንም ዓመተ ምህረት በሰላም ያሻግረን

Tuesday 21 August 2012

የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የፓትርያርክ አመራረጥ ተሞክሮ How Do We Elect A New Pope? - Your Voice TV


ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ኾነው ተመረጡ

  • ቋሚ ሲኖዶሱን የሚያጠናክሩ ብፁዓን አባቶች ተመርጠዋል::
  • ሕገ ቤተ ክርስቲያን ስለ ዐቃቤ መንበረ ፓትርያር ምን ይላል? (ከዜናው መጨረሻ ላይ ያንብቡት
    )
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 14/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 20/ 2012/ PDF)፦ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዛሬ፣ ነሐሴ 14 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀትር በፊት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ አድርጎ መርጧል፡፡ ስለዚህም ጉዳይ ዛሬ በ9፡00ሰዓት በቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡

ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ለመሠየም ምልአተ ጉባኤው ባካሄደው ምርጫ ሦስት ዕጩዎች ቀርበው እንደነበር የጉባኤው ምንጮች ለደጀ ሰላምተናግረዋል፡፡ በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 17 መሠረት ለምርጫ የቀረቡትና በሹመት ቀደምትነት ያላቸው ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት÷ ብፁዕ አቡነ ማቲያስ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሰሜን ጎንደር ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው፡፡


ቅ/ሲኖዶስ የቀብር ቀን እንዲቀየር የቀረበውን ጥያቄ አልተቀበለውም

  • የፓትርያርኩ ቤተሰቦች “በሕግ እንጠይቃለን” እያሉ ነው፤ ፓትርያርኩ የቤተሰቦቻቸው ወይስ የቤተ ክርስቲያን?
  • የሰላም እና አንድነት ጉባኤ ልኡካን አዲስ አበባ ይገባሉ፤ ጉባኤው ልዩነት በአንድነት ሳይፈታ ሌላ ፓትርያርክ የመሾሙን ጉዳይ ቅ/ሲኖዶስ እንዲያስብበት ተማፅኗል፤ የመንግሥትንም እገዛ ጠይቋል።
  • የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነትለፓትርያርኩ ሥርዐተ ቀብር አፈጻጸም ዝግጅት እያደረገ ነው።
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 15/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 21/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዜና ዕረፍት ከተሰማበት ቀን አንሥቶ አጠያያቂ ከኾኑት ጉዳዮች መካከል ሐዘናቸውን በሚገልጹ አንዳንድ ወገኖችና ብዙኀን መገናኛ ዘንድ የሚሰማው “ቤተሰቦቻቸው” የሚለው ቃል ነው፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሞት ተከትሎ የከሚሴ የጦር መሳሪያ ግምዣ ቤት በውሀቢያ ሙስሊም አክራሪዎች ተዘረፈ


·        "We are very glad about Meles' death. Ethiopia is sure to collapse,"Sheikh Ali Mohamud Rage, the spokesman for Al Shabaab told Reuters.

(አንድ አድርገን ነሐሴ 15 2004 ዓ.ም)፡- ቀናት አልፈው ቀናት ሲተኩ የሚሰማው እና የሚታየው ነገር ማህበረሰቡን እያስገረመው መጥቷል ፤ አዲስ ቀን በመጣ ቁጥር አዲስ ነገር ጠባቂ ጆሮዎች ተበራክተዋል ፤  አሁን የሰማው ግን አስደንጋጭ  ነው ፤ ሀገሪቱ በአሁኑ ሰዓት መተንፈስ እስኪሳናት ድረስ ውጥረት ውስጥ ገብታለች ፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት ፤ የፓትርያርኩ ዜና እረፍት እና ቀጣይ ከመንግስት እጅ ነጻ የሆነ የፓትርያርክ ምርጫ ፤ የተለያዩ ባለስልጣናት የጤና መታወክ ፤ በሙስሊም ማህበረሰቦች ዘንድ የተነሳው የመጅሊስ 

Friday 17 August 2012

የተቻኮለ የፓትርያርክ ምርጫ፣ ““የገበያ ግርግር …” ይሆናል


“ቤተ ክርስቲያናችን አዲስ ፓትርያርክ ከመምረጧ አስቀድሞ አሁን ከገባችበት ዝብርቅርቅ ሁናቴ ለማገገም፣ ከሐዘኗም ለመጽናናት እና አሠራሯን በሥርዓተ አበው መሠረት ለማከናወን ጊዜ ያስፈልጋታል።”
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 11/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 17/ 2012/ READ THIS ARTICLE IN PDF)፦ ቅዱስ ፓትርያርኩ እነሆ አረፉ። በብዙ እሰጥ አገባዎች የተሞላው ዘመነ ፕትርክናቸው አሁን ሌላ እሰጥ አገባ ሊፈጥር እነሆ ተፈጠመ። ነገር ግን ቤተ ክርስቲያኒቱ በመስቀለኛ መንገድ ላይ እንደቆመች ናት። ይህንን የፕትርክና ምርጫ በሰላማዊና ክርስቲያናዊ መንገድ ማካሔድ ከቻለች ብሩህ ዘመን፣ አልያም ደግሞ በግርግር እና በጥቅመኞች ፍላጎት በሚመራ አሠራር ከተከናወነም ሌላ የመከራ ዘመን ሊጠብቃት ይችላል።

Thursday 16 August 2012

የአቡነ ጳውሎስ ጳውሎስ ዜና ዕረፍት አጭር ሪፖርታዥ


  • የአቡነ ጳውሎስን ቀብር የሚያስፈጽም ኮሚቴ በመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ ጽ/ቤት ተቋቁሟል፤ መኖሪያ ቤታቸውና ቤተ መጻሕፍት ወመዘክሩ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ታሽጓል፤
  • ጥቂት ብፁዓን አበው ወደ ባልቻ ሆስፒታል ሄደዋል፤ አስከሬናቸው በባልቻ ሆስፒታል ይገኛል፤ ጥቅመኛዋ እጅጋየሁ በየነ “አልሞቱም፤ አስከሬናቸው ይመርመርልኝ” እያለች በማወክ ላይ ትገኛለች::
     ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የአድባራትና ገዳማት አለቆች በአስቸኳይ ወደ አዲስ አበባ እንዲገቡ ጥሪ ተደርጓል::
  • የአቡነ ጳውሎስን ቀብር የሚያስፈጽም ኮሚቴ በመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ ጽ/ቤት ተቋቁሟል::
  • ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ይሾማል፤ ከቋሚ ሲኖዶሱም ጋራ እየመከረ ይሠራል::(ሕገ ቤተ ክርስቲያን)
  • “ውሉደ ጳውሎስ” /እነ እጅጋየሁ በየነ/ በፓትርያርኩ ስም “ጳውሎስ ፋውንዴሽን”ለማቋቋም እየተሯሯጡ ነው፤ የሀብት ቅርምቱን ለማመቻቸት ይኾን?
  • በፓትርያርኩ በተለያዩ ዘመዶቻቸው ስም በአንድ የመንግሥታዊው ባንክ ቅርንጫፍ ሦስት አካውንቶች ውስጥ ከ22 ሚልዮን ብር በላይ እንደሚገኝ ተጠቁሟል::
(ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 10/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 16/ 2012/READ THIS NEWS IN PDF) ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዛሬ፣ ነሐሴ 10 ቀን 2004 ዓ.ም፣ ንጋት ላይ በዳጃዝማች ባልቻ ሆስፒታል ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡