Monday 27 August 2012


የዋልድባ አብረንታንት መነኰሳት መሰደድ ጀምረዋል


  • ባለፉት ጥቂት ቀናት ከስድስት ያላነሱ መነኰሳት ተሰደዋል
  • “ታጋይ ገድላችኹ እናንተ አትኖሩም” (የፀለምት - ማይ ፀብሪ ወረዳ ሓላፊዎች)።

 (ደጀ ሰላም፤ ነሐሴ 21/2004 ዓ.ም፤ ኦገስት 27/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦ በዋልድባ አብረንታንት ገዳም መነኰሳት ላይ ባተኰረውና ካለፉት አራት ቀናት ጀምሮ እየተባባሰ በቀጠለው እስርና እንግልት ሳቢያ ከስድስት ያላነሱ መነኰሳት የፀለምት - ማይ ፀብሪ የፀጥታ ኀይሎች በሚያደርሱባቸው ግፍ ሳቢያ ወደ ሌሎች ገዳማት መሰደዳቸውን፣ በተቀሩትም አባቶች ላይ ድብደባ እየተፈጸመባቸው መኾኑን የሥፍራው ምንጮች እየገለጹ ናቸው፡፡



የዜናው ምንጮች እንደሚያስረዱት÷ የወረዳው ፖሊሶችና ታጣቂዎች በገዳሙ መነኰሳት ላይ የሚፈጽሙት እንግልትና ድብደባ የተባባሰው የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ኅልፈተ ሕይወት መሰማቱን ተከትሎ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽኑ ሕመም እና ኅልፈት ገዳማውያኑን ተጠያቂ በማድረግ ነው፡፡ ቀደም ሲል በየጊዜው እየታሰሩ በተለቀቁት አበው መነኰሳት ላይ ያነጣጠረው ይኸው ርምጃ በአሁኑ ወቅት ደግሞ መነኰሳቱ ጨርሶ ገዳሙን ለቀው እንዲወጡ ከማዘዝና ከማስገደድ ጋራ የተያያዘ መኾኑም ተመልክቷል፡፡

በወረዳው የጸጥታ ኀይሎች “ገዳሙን ለቃችሁ ውጡ፤ ታጋይ ገድላችሁ እናንተ በሰላም አትኖሩም፤” እየተባሉ መደብደባቸውን የተናገሩት የዋልድባ አብረንታንት መነኰሳት÷ በተለይም ከነሐሴ 18 ቀን 2004 ዓ.ም በሚፈጸምባቸው ድብደባ በርካታ አባቶች መጎዳታቸውን፣ ከተሰደዱት ስድስት መነኰሳት መካከልም አባ ገብረ ማርያም ጎንዴ እና አባ ገብረ ጊዮርጊስ የተባሉ አባቶች እንደሚገኙበት አስታውቀዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ማኅበረ መነኰሳቱ ከሰኔ 21 ቀን እስከ ኅዳር 8 ድረስ በሚዘልቀው የሱባኤ ወቅት ላይ ይገኛሉ፤ የመንግሥት ሓላፊዎችም በተለመደው አነጋገር “ዳዊታቸውን እንደ ዘቀዘቁ ናቸው፤ መቅሠፍቱም ይቀጥላል” ብለዋል በሚል የገባው በማይወጣበት፣ የወጣው በማይገባበት ይህን የሱባኤያቸውን ወቅት እንኳ ሳይታገሡ ነው ድብደባውንና እንግልቱን የሚፈጽሙት፡፡

በአቶ መለስ መሐንዲስነት እንደተቀየሰ በተነገረው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውስጥ የአንዱስትሪ ልማት ዘርፍ አካል ከሆኑት ዐሥር ግዙፍ የስኳር ፋብሪካ ግንባታዎች አንዱ የኾነው የወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት÷ በገዳሙ ህልውናና ክብር ላይ ከሚያደርሰው ተጨባጭ አደጋና ታሳቢ ስጋቶች የተነሣ ሐዘናቸውን ወደ እግዚአብሔር በማመልከት የቆዩት አበው መነኰሳት የዋልድባ አብረንታንት ገዳም ዘቤተ ሚናስ ማኅበር አባላት ናቸው፡፡

ነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም ከሌሊቱ 5፡40÷ በሚኒስትሮች ም/ቤት መለጫ መሠረት ድንገት በተከሠተ ኢንፌክሽን÷ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው የተሰማው የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጽኑ ሕመምና ኅልፈት “የመነኰሳቱ እንባና ሐዘን ወደ እግዚአብሔር ከመድረሱ የተነሣ የመጣብን ተግሣጽ ነው” ብለው የሚያምኑ ወገኖች ቁጥር በቀላሉ የሚገመት እንዳልሆነ በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች የሚታዩ የመረጃ ልውውጦች እና ከኅልፈታቸው ጋራ ተያዘው የሚደመጡ ፈርጀ ብዙ ትርክቶችእያጠየቁ ናቸው፡፡

ቸር ወሬ ያሰማን፤
አሜን፡፡
Anonymous said...
“የመነኰሳቱ እንባና ሐዘን ወደ እግዚአብሔር ከመድረሱ የተነሣ የመጣብን ተግሣጽ ነው” ብለው የሚያምኑ ወገኖች ቁጥር በቀላሉ የሚገመት እንዳልሆነ በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች የሚታዩ የመረጃ ልውውጦች እና ከኅልፈታቸው ጋራ ተያይዘው የሚደመጡ ፈርጀ ብዙ ትርክቶች እያጠየቁ ናቸው፡፡
Anonymous said...
“ዳዊታቸውን እንደ ዘቀዘቁ ናቸው፤ መቅሠፍቱም ይቀጥላል”
hailu said...

Meche yihon yihe giff yemiabekaw?

Lemins balesilatanochu libachewun ende Feron adenedenut?

Sew behageru, emnetun tebiko,hulun tito begedam menor ayichilim?

Gifachewun eskeketelu dires Egziabher seifun yizeregal.

They keep messing with Waldiba, the Woyanes will follow suit with Aba Paulos, Meles, etc.
Anonymous said...
Abetu Amkak Hoy Tebake Melakhen lakelegn ale Kidus Dawit on the last Psalm.

Abetu Amlak Hoy YekerBelen!!! Abetu Amlak Hoy begochehen tebek ebakeh.
Kebede Bogale said...
ኦሪት ዘጸአት ላይ ተጽፎ ያለውን የፈርዖንና የሙሴን ታሪክ አየደጋገምኩ እንዳነበው ይህ በዋልድባ ገዳም መነኮሳትና በወያኔ /ኢሐደግ መካከል ያለው ሁኔታ አስገደደኝ። በቤተ ፈርዖን ስንት አይነት መቅሰፍቶች ነበረ የተላኩበት ? መጨረሻስ በ1270 ከክርስቶስ ልደት በፊት በማን አሸናፊነት ድርጊቱ ተፈፀመ ?
Anonymous said...
I always ask what happened to us (Tewahedo Christian believers)? When are we getting mad and rise up for our right and our true faith? How long we just keep on reading this kind of story and do nothing about it except just feel sorry?

Oh God! Please give us strength and help us to stand for our church. Amen!
Anonymous said...
Ene yemilew? Egzer endi miketa bihon weym mot mkchaw bihon engdia egna zelalemawyan nena!Tewu poleticanina haymanotin atkeytu. Lemehonu ezaw gedamu wust ersbers slslew rejim gize yekoye kififilna ersbers dibdib takalachu? Engdia Egzer endet yhin zim ale? Antenna enens bezihulu hatyatachin endet tagesen? Ene bebekule maninim altelam. beteley kemotu behuwala sile PMu yesemahuwachew negeroch betam germewgnal. Tewu keEgzer wenber enwred? Bebekule mekseft kale yemejemeryaw mekseft yemigebagn ene negn.Enantes yedejeselam azegajochina anbabiwoch, tsadkanina yaltekesefachut kemotut wegenoch silemitshalu yhon? Lib ysten.
Anonymous said...
Ye mimeka be Egziabeher yemeka. Enezihe aheyoch begulbetachew temeketewal. God is going to judge on that, which is already known that He decided and there time is up. Years ago there was a vision seen that meles and his groups going up in the sky like a rocket going to the moon, but fall like a winter tree to the ground on it's own with out nobody touching it. Actually that is what happned the past few days. Thanks to the great God of the poor and oppresed. No worries the Waldibas are Semaetat.
Anonymous said...
"Ene yemilew?" yalkew wendeme/ehete esti nigeregn. Koy enezih menekosat letedebedebut, leteseqayut mene hazenete satasay ledebdabiwochu mazeneh meen yebablal? Yehe neew Cristiyanawi feqer malet? Le Dawit sayhon Le Goliyad mazen?
Anonymous said...
Kadrewoch Ke Egziabher gar megedaderu bibekachewu min ale!? Ere betekirstianin lekek adrguat. Yekirstos bet titilalechi enji befisum atwodkm.

No comments:

Post a Comment