Wednesday, 25 July 2012

ውድ የእንደማመጥ አንባቢያን


ይህቺ ድረ ገጽ የተጀመረችበት ዋና አላማ ኢትዮጵያ ውስጥ ደጀ ሰላም እና አንድ አድርገን በፓትርያርኩ ግብረ አበሮች እና በመንግስት አማካኝነት እንዳይነበቡ በመደረጋቸው የተፈጠረውን የመረጃ ክፍተት ለመሙላት ነው። 
በእርግጥ ተራዋ ደርሶ እርሷም መዘጋቷ አይቀርም ሆኖም ግን እስከዛው ድረስ ስለቤተክርስትያን አጥብቀው ማወቅ መስማት ለሚፈልጉ ወንድም እና እህቶች በሚስጥር መልእክት  (PRIVATE MESSAGE) በመለዋወት መንፈሳዊ እና ታሪካዊ ግዴታችንን እንወጣ። 


ማሳሰቢያ
እባክዎን በፌስቡክ ገጽዎ ወይም ግሩፕ ላይ(share) እንዳያደርጉ
ሰላመ እግዚአብሄር ከሁላችን ጋር ይሁን አምላከ ቅዱሳን ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን 




የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የፓትርያርክነት ማዕርግ የተቀዳጀችበት የነጻነት በዓል - በዓለ ሢመተ ፓትርያርክ - አከባበር የመንፈሳዊ ውርደትና የምዝበራ መንገድ ኾኗል




(ደጀ ሰላም፤ ሐምሌ 16/2004 ዓ.ም፤ ጁላይ 23/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦ በሙስና፣ ብኵንነት፣ ኑፋቄ እና ዐምባገነናዊ አሠራር የነቀዘው የአባ ጳውሎስ ዘመነ ፕትርክና 20 ዓመት በዓለ ሢመት ዛሬ ምሽት ለሁለተኛ ጊዜ በሼራተን አዲስ ይከበራል። የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት እና ራእይ ለትውልድ /Vision for Generation/ የተባለው አካል የጥቅም ትስስር የፈጠሩበት የሼራተኑ በዓለ ሢመት ዝግጅት በቅ/ሲኖዶስ ጽ/ቤት ይኹን በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጽ/ቤት አይታወቅም።


የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የአብያተ እምነት መሪዎች፣ አምባሳደሮችና ታዋቂ ግለሰቦችን ጨምሮ እስከ 1500 እንግዶች ይታደሙበታል በተባለው ይኸው ዝግጅት ከጥቅም ትስስር ባሻገር÷ በግንቦቱ ቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ እና ውሳኔዎች ክፉኛ የተጋለጠውን የአባ ጳውሎስን ማንነት ለማደስ የታሰበበት ‹የሕዝብ ግንኙነት› ሥራ እንደኾነ ተጠቁሟል። በበዓለ ሢመቱ አከባበር የቀደሙት ፓትርያርኮች መልካም ስምና ዝና በተለያዩ ስልቶች እየተንኳሰሰ በምትኩ በሙስና፣ ኑፋቄ እና ዐምባገነናዊ አሠራር የተበሳበሰው የአባ ጳውሎስ ዘመነ ፕትርክና የሥራ ክንውን ብቻ “በወደር የለሽነት” /በእንግሊዝኛው የበዓለ ሢመት ኅትመት ላይ እንደተገለጸው - ‘unparalleled efforts/ እንደ ግለሰብ መሞገሱ ብዙዎችን አሳዝኗል።


“ሙስሊም ወንድማማቾች የፖለቲካ ፓርቲ” ለመመስረት ጥያቄ መቅረቡ ተሰማ


  •   መንግስት በጥያቄው ደንግጧ
  •    “ ማንኛውም ሰው ለማንኛውም ዓላማ በማህበር የመደራጀት መብት አለው ፡፡” የኢትዮጵያ ህገ መንገስት አንቀጽ 31

(አንድ አድርገን ሐምሌ 18 2004 ዓ.ም)፡- የሀገሬ ሰው “የባሰ አለና ሀገርህን አትልቀቅ” ይላል ፤  በአሁኑ ሰዓት  እንዲህማ አይታሰብብ የምንለው ጉዳይ እንደ ትልቅ ጉዳይ ብቅ ብሏል ፤ ይህ ጥያቄ ውስጠ ወይራ ነው ፤ መንግስት የሚደሰኩርለትን ዲሞክራሲን መሰረት አድርጎ የውስጥን አላማ ለማሳካት የተነሳ ጥያቄ ፤ ካለመጠይቅ ደጃዝማችነት ይቀራል በማለት የተነሳ ወቅታዊ ጥያቄ ፤ ሙስሊሙን ነጻ አወጣለው በማለት የሙስሊምን የበላይነት ለማረጋገጥ ሲባል የዘመናት ጥያቄዎቻውን ለመመለስ ያመቻቸው ዘንድ የጠየቁት ጥያቄ ፤ ……


መወቀር - በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ


ክርስትና ሰዉነት ለክርስቶስ ማደሪያ መቅደስነት የተሠራበት የድኅነት መንገድ ነው፡፡ሰው በነፍሱ ወይም ከትንሣኤ በኋላ ባለው ሕይወቱ ብቻ ሳይሆን በዚህ ምድር በሚኖርበት ጊዜም ሰዉነቱ የክርስቶስ ማደሪያ መቅደስ፣ኅሊናዉ ቃሉ የተቀረጸበት ጽላት፣ ልቡናዉም  የበጎ ነገር ሁሉ ማደሪያ ታቦት እንዲሆን የተዘጋጀ ነዉ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ‹‹ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?...  ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ›› /1ኛ ቆሮ 6፤ 13- 19/ ሲል እንደገለጸልን ሰዉነታችን ለእኛ ፍላጎት ማከማቻነት የተዘጋጀ ቁምሳጥን ሳይሆን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመፈጸም የተሰጠን ቅዱስ ንዋይ ነው፡፡ ሐዋርያዉ እንደገለጸዉ ገንዘብነቱም ለእግዚአብሔር ነዉ፡፡  አገልግሎቱም እግዚአብሔርን ማክበር ነው፡፡

Monday, 23 July 2012

“የአቡነ ጳውሎስ ገድል” በ20ኛ በዓለ ሢመት መጽሀፍ


  • ባለፉት 20 ዓመታት በወር በአማካይ 28 ቤተክርስትያኖችን አቡነ ጳውሎስ እንዳሰሩ ይገልጻል (በ20 ዓመት 6800 ቤተክርስትያናት ተስርተዋል ይለናል)

(አንድ አድርገን ሐምሌ ሚካኤል ፤ 2004 ዓ.ም)፡- አንጸባራቂዎቹ 20 ዓመታትን በማስመልከት በጠቅላይ ቤተክህት አንድ መጽሀፍ ተዘጋጅቶ ነበር ፤ ይህን የአቡነ ጳውሎስን ገድል የሚተርክ መጽሀፍ ለማሳተም በርካታ ሺህ ብሮች እንደወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ ፤ የመጽሀፉ አዘጋጆች ምዕመኑ በብር ግዛ ቢባል እንደማይገዛ በማወቃቸው በሺህ የሚቆጠሩ መጻህፍትን በነጻ ሲያድሉ ተመልክተናል ፤ ሐምሌ 5/2004 ዓ.ም አራት ኪሎ ቅድስት ስላሴ ቤተክርስትያን ከመንግስት የተጋበዙ ባለስልጣኖች ፤ የውጭ ጥቂት ዲፕሎማቶች ፤ ፈቅደው ሳይሆን ከየደብሩ የመጡ ካህናትና መዘምራን ፤ ብዛት ያላቸው ጳጳሳት የተገኙበት ስርዓት ነበር፡፡ ምዕመኑ ከ150 የማይበልጥ ሲሆን አብዛኛው ቦታውን የያዙት ተጋባዥ እንግዶች ነበሩ ፤ መሀል ላይ ያለው 10 ሜትር የሚያህል ቦታ ዳር ዳር የቆሙት ምዕመናን ለመታዘብ እንጂ በዓለ ሲመታቸውን ለማክበር የመጡ አይመስሉም ፤ የቅድስት ስላሴ የፊት ለፊቱ ደረጃ በቅጡ በምዕመኑ መሙላት አቅቶት አስተውለናል ፤ አቡነ ጳውሎስ በስተቀኝ እነ ተስፋዬ ውብሸትን ከበስተኋላ ዲፕሎማቶችን ፤ ከበስተቀኝ ደግሞ ሊቃነ ጳጳሳትን አስቀምጠው መሀል ቁጭ ብለዋል፤  በነጻ የሚታደለውን መጽሀፍ በግራ እና በቀኝ የሚያድሉ ሰዎች ተሰማርተው ሰው እጅ ላይ የማድረስ ስራቸውን ተያይዘውታል ፤ ፕሮግራም መሪው የአቡነ ጳውሎስን ፤ የተጋባዥ የመንግስት ባለስልጣናትን ፤ አምባሳደሮችን ስም ሲጠራ ለሰማ ምንድነው ይህ ሁሉ የመዓረግ ጋጋታ ማለቱ አይቀርም ፤የነሱ ስምና መዓረጋቸው ብቻ ከአንድ ገጽ ቢበልጥ እንጂ አያንስም ፤ የሚነበበውን ነገር ጆሮ ሰጥቶ የሚያዳምጥ ሰው ማግኝት መታደል ይመስላል ፤ ማን እንደሚያነብ ስለምን እንደሚነበብ ፤ የጽሁፉ መልዕክትና ይዘት የነበረው እንግዳ ቢጠይቁ ከመቶ አምስቱ አይመልስሎትም ፤ በጣም አሰልቺ ከመሆኑ የተነሳ አንድ ሰው እስከ 5 ገጽ ያነበበበትም ጊዜ ነበር ፤ አቡነ ጳውሎስ አስከ አሁን የሰሩት ወይም ወደፊት የሚሰሩት ስራ አሳስቧቸው ነው መሰል እርሳቸውም ንግግሩን በአጽንዎ እየተከታተሉ አይደሉም ፤ ታዲያ ይህ በዓለ ሲመት ለማነው የተዘጋጀው? የሚያስብል ሁኔታን ይመለከታሉ ፤ እኛ እንኳን የመጣነው 4 ኪሎ ስላሴ ቤተክርስትያን ግቢ ውስጥ እንደ ቦሌው ሌላ ሃውልት ካቆሙ ሃውልቱን ለማፍረስ እንጂ መርሀ ግብሩን ለመሳተፍ አልነበረም ፤ ማን ያውቃል ሀውልቱን እንደማይደግሙት ? 

የሲያትል ምእመናን አቡነ ፋኑኤልን በይፋ ተቃወሙ፤ እንዳይመጡም ተስማሙ


(ደጀ ሰላም፤ ሐምሌ 10/2004 ዓ.ም፤ ጁላይ 17/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦ በሰሜን ምዕራብ አሜሪካ በዋሺንግተን ሲያትል በሚገኙት  በደብረ ሰላም ቅ/ሚካኤል እና በደብረ መድኃኒት ቅ/አማኑኤል አብያተ ክርስቲያናት በድብቅ ሊመጡ ያሸመቁትን አቡነ ፋኑኤልን ሕዝቡ በይፋ ተቃወመ፡፡ እሑድ ከቅዳሴ በኋላ ምእመናን በይፋ ባቀረቡት ጥያቄ ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ሕገ ወጡ ሊቀ ጳጳስ አባ ፋኑኤል ወደ አብያተ ክርስቲያናቱ እንዳይመጡ በብርቱ ተቃውሞ ቀርቧል። በሌሎች አካባቢዎች የተጀመረው “ቤተ ክርስቲያንን ከነአባ ፋኑኤል እና ከፕሮቴስታንቱ አጋራቸው ከኃ/ጊዮርጊስ ጥላሁን የመታደግ” እንቅስቃሴ በሲያትልም ተጀምሯል። “ምንም አያውቅም” እየተባለ የሚናቀው ምእመን ለቤተ ክርስቲያኑ የክፉ ቀን ደራሽ መሆኑን እና በሐዋሳ ያለው ሕዝበ ክርስቲያን እንባውና በተጋድሎው ቅ/ሲኖዶስ ኡኡታውን ሰምቶ ያገኘውን ድል በአሜሪካ የሚገኘውም ምእመን እንደሚደግመው አረጋግጧል።


የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የፓትርያርክነት ማዕርግ የተቀዳጀችበት የነጻነት በዓል - በዓለ ሢመተ ፓትርያርክ - አከባበር የመንፈሳዊ ውርደትና የምዝበራ መንገድ ኾኗል



(ደጀ ሰላም፤ ሐምሌ 16/2004 ዓ.ም፤ ጁላይ 23/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦ በሙስና፣ ብኵንነት፣ ኑፋቄ እና ዐምባገነናዊ አሠራር የነቀዘው የአባ ጳውሎስ ዘመነ ፕትርክና 20 ዓመት በዓለ ሢመት ዛሬ ምሽት ለሁለተኛ ጊዜ በሼራተን አዲስ ይከበራል። የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት እና ራእይ ለትውልድ /Vision for Generation/ የተባለው አካል የጥቅም ትስስር የፈጠሩበት የሼራተኑ በዓለ ሢመት ዝግጅት በቅ/ሲኖዶስ ጽ/ቤት ይኹን በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጽ/ቤት አይታወቅም።


የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የአብያተ እምነት መሪዎች፣ አምባሳደሮችና ታዋቂ ግለሰቦችን ጨምሮ እስከ 1500 እንግዶች ይታደሙበታል በተባለው ይኸው ዝግጅት ከጥቅም ትስስር ባሻገር÷ በግንቦቱ ቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ እና ውሳኔዎች ክፉኛ የተጋለጠውን የአባ ጳውሎስን ማንነት ለማደስ የታሰበበት ‹የሕዝብ ግንኙነት› ሥራ እንደኾነ ተጠቁሟል። በበዓለ ሢመቱ አከባበር የቀደሙት ፓትርያርኮች መልካም ስምና ዝና በተለያዩ ስልቶች እየተንኳሰሰ በምትኩ በሙስና፣ ኑፋቄ እና ዐምባገነናዊ አሠራር የተበሳበሰው የአባ ጳውሎስ ዘመነ ፕትርክና የሥራ ክንውን ብቻ “በወደር የለሽነት” /በእንግሊዝኛው የበዓለ ሢመት ኅትመት ላይ እንደተገለጸው - ‘unparalleled efforts/ እንደ ግለሰብ መሞገሱ ብዙዎችን አሳዝኗል።

“ማኔ ቴቄል ፋሬስ” ብሎ የሚጽፈው ጣት እንዳይቀርብባችሁ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ


(አንድ አድርገን ሰኔ 13 ፤ 2004 ዓ. ም)፡- በአሁን ወቅት ጆሯችን የሚሰማው ፤ ከጋዜጦች የምናነበው ፤ ከድህረ ገጾች የምንመለከተው ነገር የጠቅላይ ሚኒስትሩን መታመም የሚያመላክቱ ምንጫቸው ከተለያዩ ቦታዎች የሆኑ መረጃዎችን ነው ፤ በትላንትናው እለት የመንግስት ኮሙኒኬሽን ሚኒስትር አቶ በረከት ስምኦን ትንሽ የጤና እክል እንዳጋጠማቸው ከሀኪም እረፍት በኋላ በጥቂት ቀናት ውስጥ ወደ ስራ እንደሚመለሱ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል ፤ ከአንድ ቀን በፊት አቶ ስብሀት ነጋ በፌዝ በቪኦኤ እንደተናገሩት “በሚቀጥሉት 10 ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚንስትሩ ወደ ስራ ገበታቸው ይመለሳሉ” ብለዋል ፤ አይይ…ሰው ከተያዘ በኋላ ፌዝ ምን ይሰራል ? ነገረር ግን ደህና ሆነው ከ10 ወር በኋላም ቢመለሱ መልካም ይመስለናል ፤ ዋናው ጤና ነው ፤ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ስራ መሆኑን እስከ አሁን አናውቅም ነበር ፤ ይገርማል ፤ ለካ የመንግስት ተቀጣሪ ናቸውን ? ሰው በህይወት ዘመኑ በተለያዩ አጋጣሚዎች በሽታዎች ይጎበኙታል ፤ በቀላሉ ደረስ መለስ የሚሉ ህመሞች እንዳሉ ሆነው ከሰው እድሜ ጋር 


የተሃድሶያውያኑ ቀበሮ መነኩሴ

  • የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ  የማቴዎስ ወንጌል 715
(አንድ አድርገን ሐምሌ 16 2004 ዓ.ም)፡- ትምህርተ ሃይማኖቷ እምነቷና ሥርዐቷ ምሉዕ የሆነውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፤ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ርትዕት ሃይማኖት «እናድሳለን» በሚል ስልት ወደ ውስጧ ሠርጐ በመግባት ልጆቿን እስከ ሕንፃ ቤተክርስቲያኗ እንረከባለን ይላሉ፡፡ የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎቻቸውን በማሰማራት በጎቿን በኑፋቄያቸው እያሳሳቱ ከመንጠቅ፣ በተለያዩ ርዳታዎች ስም እየደለሉ ከማስኰብለል ጀምሮ፤ ትምህርተ ሃይማኖትና ሥርዐቷን በማጣጣል፣ ቅዱሳት መጻሕፍቷን በማራከስ፣ መልካም ስምና ገጽታዋን በማጠልሸት የሚያደርጉት የጥፋት ጥረታቸው ዛሬም እንደቀጠለ ነው፡፡ በእናትነት እቅፏ ውስጥ ጡቷን ጠብተው ማዕዷን ተሳትፈው አድገው፤ ነገር ግን ንጹሕ እናትነቷን ክደው በውስጧ ሆነው በኑፋቄያቸው የሚቦረቡሯት ብዙዎች ናቸው፡፡ 

Saturday, 21 July 2012

በዋልድባ መነኰሳት ላይ የሚካሄደው እስርና እንግልት ተባብሶ ቀጥሏል


  • አንድ የዋልድባ አብረንታንት ገዳም መነኰስ ወደ ማይ ፀብሪ ተወስደዋል።
  • የገዳሙ መነኰሳት የግዴታ መታወቂያ እንዲወስዱ ተደርገዋል።
  • ፓትርያርኩ ዕግድ የጣሉበት የጀርመን የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሒዷል።
(ደጀ ሰላም፤ ሐምሌ 14/2004 ዓ.ም፤ ጁላይ 21/ 2012/ READ THIS NEWS IN PDF)፦ የወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት በዋልድባ ገዳም ህልውናና ክብር ላይ በሚያደርሰው ተጨባጭ አደጋና ታሳቢ ስጋቶች የተነሣ የፕሮጀክቱን አተገባበር በሚቃወሙ የዋልድባ ማኅበረ መነኰሳት ላይ የሚደርሰው እስር፣ እንግልትና ድብደባ ተባብሶ መቀጠሉን የሥፍራው ምንጮቸ ለደጀ ሰላም ገልጸዋል፡፡ በተለይም የፀለምት - ማይ ፀብሪ ወረዳ አስተዳደር በየጊዜው በመነኰሳቱ ላይ በሚወስደው የግፍ ርምጃ በሠቆቃ ውስጥ የሚገኙት ማኅበረ መነኰሳቱ ከሰኔ 21 - ኅዳር 8 ቀን የሚዘልቀው የገዳሙ የሱባኤ ወቅት እንደታወከ ተዘግቧል፡፡