Thursday, 5 July 2012


ርዕሰ አንቀጽ፡- የሀገሪቱን ሰላም ለማስከበር የቤተ ክርስቲያኒቱን ሰላም ማስከበር



(ደጀ ሰላም፤ ኤፕሪል 2/2011)፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለኢትዮጵያ ያበረከትችውን አስተዋጽዖ መዘርዘር ለቀባሪው እንደማርዳት ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተለይ ሕግና ሥርዓትን አውጥታ፤ ካህናትና ምዕመናን በአንድነትና በመከባበር የቤተ ክርስቲያኒቱን ሥርዓተ እምነት፤ ዶግማና ቀኖና እንዲጠብቁና እንዲያስጠብቁ፤ በልማትና በማኅበራዊ ጉዳዮች በሕብረተሰቡ ዘንድ መረዳዳትና መቻቻል እንዲኖር አድርጋለች፣ በማድረግም ላይ ትገኛለች። ይህም ለሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጓል።

ስት ቤተ ክርስቲያን እነዚህን ሁሉ ተግባራት ለዘመናት ስታከናውን የቆየችው በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ያለው መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረድ በመጠቀምና በማክበር ነው። ይህም አራር ለዘመናት ሳይፋለስ ቆይቷል። ይህንን ከሀገሪቱ ከ50% በላይ የሆነና በሚሊዮን የሚቆጠር ምዕመን ይዛ በሕግና በሥርዓት ባታስተዳድር ኖሮ የቤተ ክርስቲያንቱ ሰላም ብቻ ሳይሆን የሀገሪም ሰላም ሊደፈር እንደሚችል እሙን ነው። የቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረድ ለማስጠበቅ እና በቤተ ክርስቲያንቱ አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ለሚወሰኑ ውሳኔዎች ተፈፃሚነት የግ ከለላ በመስጠት በየጊዜው የነበሩት ነገታትና የመንግሥት  አካላት በቂም ባይሆን የበኩላቸውን አስተዋጽዖ አበርክተዋል።

ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት የቤተ ክርስቲያቱን ዶግማና ቀኖና ለማፍረስና ብቷንና ንረቷን ለመዝረፍ እንዲያመ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረዷን መጣስ እየተለመደ መጥቷል። እነዚህን ሕገ ወጥ ተግባራት ለመከላከል የቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ ጠባቂና ወሳኝ አካል የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ እና በየደረጃው ያሉ እውነተኛ የቤተ ክርስቲያን አመራር አካላት የሚወስኗቸው ውሳኔዎችና አመራሮች ተግባራዊ እንዳይሆኑ ብዙ እንቅፋቶች እያጋጠሟቸው ነው። ለዚህም እንደማሳያነት በቦሌ የቆመው የፓትያርኩ ሐልተ ስምዕ መፍረስና በሐዋሳ ሀገረ ስብከት በተፈጠሩ ችግሮች ላይ የተወሰኑት ውሳኔዎችን ለማስፈፀም ያለው ፈተና መግለፅ ይቻላል። ከዚህ አንጻር ስንመለከተው፦

1.      የቤተ ክርስቲያንቱን ዶግማ፤ ቀኖና እና ትውት ለማስከበር እና የቤተ ክርስቲያንን ብት እና ንብረት ከውድመትና ከዝርፊያ ለመታደግ ጥረት በሚያደርጉ አባቶች ላይ እየተደረገ ያለው ዛቻ፤ ጫና እና ማስፈራሪያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የሚገኝ ጉዳይ እንጂ የሚቀንስ ሆኖ አለመገኘቱ፤ ይህም ጉዳይመንግሥት  በሀገሪ የለም፤ ሕግና ሥርዓት አስከባሪ የለም፣ መንግሥት ለቤተ ክርስቲያኒቱ ደንታ የለውም”’ እስከኪባል ድረስ አድርሶታል።

2.     ባለፈው ዓመት በተደረገው በብፁዓን አበው ላይ የደረሰው ድብደባ፤ አፈናና ዛቻ የፈፀሙት ግለሰቦች ለፍርድ አለመቅረብና ሕጋዊ ቅጣት አለማግኘት ምዕመኑ በመንግሥት  ላይ ያለውን ተስፋ እስከመጨረሻው እንዲሟጠጥ አድርጎታል።

3.     በዚህ ዓመትም በጥቅምት ወር በተደረገው ጉባኤ ላይም ቢሆን ብዙ ብፁዓን አባቶች የማስፈራሪያ ዛቻዎች በስልክ እና በአካል ተሰንዝረዋል። አሁንም የቤተ ክርስቲያቱ ዶግማና ቀኖና እንዲጠበቅ፤ ብቷ እና ንብረቷ እንዳይዘረፍ፤ እና የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረድ እንዲጠበቅ በሚታገሉ አባቶች ላይ ከእነዚህ ቡድኖች የሚሰነዘረው ማስፈራሪያ ቢጨመ እንጂ አልቀነሰም። 
  
4.     በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በቅዱስ ሲኖዶሱ የተወሰኑት ውሳኔዎችንም ለማስፈፀም አለመቻሉ በቤተ ክርስቲያቱ ውስጥ ነው በዝርፊያና የቤተ ክርስቲያን ሰላም በማደፍረስ ምዕመኑን ተፋ በማስቆረጥ ራ ላይ የተሰማሩት ቡድኖች ቤተ ክርስቲያኒቱ ብሎም በሀገሪ ሰላም እና ልማት ላይ ከፍተኛ አደጋ እንደሚጥሉ ማወቅ ማስረጃና ጥልቅ ምርምር አያሻውም።
5.     አሁንም ቢሆን መንግሥት በራሱ የሚያደርገውን አስተዳደራዊ በደል ምዕመኑ የሚታገሰውን ያህል በእምነቱ ሲመጣበት ሊታገስ እንደማይችልና የቤተ ክርስቲያ ዶግማና ቀኖና እንዲጠበቅ፤ ብቷ እና ንብረቷ እንዳይዘረፍ፤ እንዲሁም የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረድ እንዲጠበቅ አስፈላጊውን መስዋዕትነት መክፈል እንደሚችል አውቆ መንግሥትያስብበት ይገባል

6.     በፖለካው ረገድ በቅርቡ በሰሜን አፍካ በኢ-ፍትሐዊ አስተዳደሮች ላይ የተደረገው ዓይነት ሕዝባዊ አመ ለመሪዎች መባረ ምክንያት እንደሆነው ሁሉ ይህ በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚደረገው በደል ማቆም ካልተቻለ በኢትዮጵያ ምዕመ ወደዚህ ዓይነት ቁጣ ሊራመድ እንደሚችል መንግሥት ሊረዳው ይገባል።

7.     ስለሆነም የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ የልጣን ተዋረድ እንዲጠበቅ እና በቤተ ክርስቲያንቱ የበላይ ጠባቂና ወሳኝ አካል በሆነው በቅዱስ ሲኖዶስ እና በየደረጃው ባሉ እውነተኛ የቤተ ክርስቲያን አመራር አካላት የሚወሰኑት ውሳኔዎችና አመራሮች በእምነቱ ቀኖናዊ አራር መረት ተፈሚ እንዲሆኑና ከላይ ለተጠቀሱት ለእውነተኛ የቤተ ክርስቲያንቱ አካላት መንግሥት  አስፈላጊውን የግ ከለላሰጥ ይገባል እንላለን።

8.     መንግሥት የሀገሪቱን ሰላም ለማስከበር የቤተ ክርስቲያኗን ሰላም ማስከበር ይጠበቅበታል

ቸር ወሬ ያሰማን፣ አሜን

No comments:

Post a Comment