ሰኔ 15 ቀን 2004 ዓ.ም እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በዓለ ልደት አደረሳችሁ::
በዘሚካኤል አራንሺ
በዮሴፍ ወልደ ያዕቆብ ዘመን የነበረው ፈርኦንና የመጥምቁ ዮሐንስን አንገት ለዘፋኝ ወሮታ የሰጠው ሄሮድስ የሚያመሳስላቸው አንድ
ዓይነት ተግባር ፈጽመዋል:: ይኽውም ሁለቱም ልደታቸውን ያከብሩ እንደነበር በመጽሐፍ ቅዱስ መጠቀሱ ነው:: /ዘፍ.40፥20 ፤
ማቴ.14፥6/:: ታሪካቸውን ስናጠና ደግሞ በርካታ መመሳሰል እንደነበራቸው እንገነዘባለን:: ሁለቱም ነገሥታት ናቸው:: ሁለቱም
ንጹሐንን አስረዋል:: ሁለቱም ደም አፍሳሾች ነበሩ:: በልደት በዓላቸውም ነፍስ አጥፍተዋል:: በልደት በዓላቸው ነፍስ ያጠፉ
ሰዎች ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ መጻፉ የልደት በዓል ማክበርን ስህተት አያደርገውም:: በጌታችን ልደት መቶ አርባ አራት ሺህ
ሕጻናት በሄሮድስ ትእዛዝ ተገድለዋል:: የጌታችንን ልደት ግን እናከብራለን:: መግደል ኃጢአት መሆኑን እንመሰክርበት ካልሆነ በቀር
ነፍስ በማጥፋት የሚከበር በዓል የለንም:: የፋሲካን በዓል በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ለማክበር እንገደዳለን እንጂ ዘፋኞች ድግስ
ስለሚያዘጋጁበት ማክበሩ ቢቀር ቢባል ሞኝነት ነው:: ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን የቅዱሳንን ልደት በዓል ስታከብር የራሷ
ሥርዓትና ባሕል የበዓላት መቁጠሪያ /ሊተርጂካል ካላንደር/ አላት:: የቱ መቼ መከበር እንዳለበትም ምክንያታዊ በሆነ መንገድ
ታስረዳለች:: ጥንታዊት ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆንዋም በርግጥኝነት ዕለታቱን ቆጥራ ትናገራለች:: በነቢይ የአዋጅ ነጋሪ
ቃል ተብሎ የተነገረለት የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስን የልደት በዓል የምታከብረው በሰኔ ሠላሳ ቀን ነው::
የጻድቃን ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ እንደሆነ፤ ቅዱሳኑን ያገኘንባት ልደታቸውም የከበረች ናት:: /መዝ.116፥15/::
የመጥምቁ ዮሐንስን ልደት ያበሰረው መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል “በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል::” እንዳለ በልደተ ቅዱሳን ደስ
እንሰኛለን:: /ሉቃ.1፥14/:: በዓለ ቅዱሳን የደስታ በዓላት ናቸውና:: የተወለዱበት ፥ ልዩ ልዩ ገቢረ ተዓምራት ወመንክራት
የፈጸሙባቸው፥ ሰማእተ ኢየሱስ ሆነው መከራ የተቀበሉባቸው፥ያረፉበትና የተሰወሩበት፥ ቃል ኪዳን የተቀበሉባቸውን ዕለታት
የምናከብረው በደስታ ነው:: ቅዱስ ዳዊት “ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ምስጋና መኖሪያ ስፍራ እገባለሁና በዓል የሚያደርጉ ሰዎች
የደስታና ምስጋና ቃል አሰሙ።” እንዲል:: /መዝ.42፥4/:: ዕለታቱ በደንጊያ ተወግረው፥ በመጋዝ ተተርትረው ፥ ወደ እሳት
ተጥለው፥ ለአናብስት ተሰጥተው፥ በሰማእትነት ያረፉባቸው እንኳ ቢሆኑ የደስታ በዓላት ናቸው:: የምስክርነታቸውን እውነትነት፥
የእምነታቸውን ጽናት፥ ታዛዥነታቸውንና ለአምላካቸው ያላቸውን ፍቅር በመግለጣቸው፤ የሚያገኙትን ክብር፥ የሚወርሱትን
መንግስት እናስባለንና:: የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅን የከበረች የእረፍቱን ቀን በማኅሌት ከበሮ መትተን፥ጸናጽል ጸንጽለን፥ ወረብ
ወርበን፥ ቅዳሴ ቀድሰን፥ መዝሙር ዘምረን፥ መልክ ደግመን፥ ገድል አንብበን፥ ተዓምሩን ተናግረን፥ ቅድስናውን መስክረን
እንደምናከብረው በዓለ ልደቱንም እንዲሁ እናከብራለን:: ጠቢቡ “ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል...” ብሏልና::
በመወለዳቸው ደስ ተሰኝተን በዓል እናደርጋለን:: /ምሳ.29፥2/::ካህኑ ዘካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥ የብዙዎችን ደስታ ወልደዋል::
ጌታችን በወንጌል “መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፥ . . . ” /ማቴ.7፥17-19/:: በማለት እንዳስተማረን የመጥምቁ
ወላጆች “በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ” ተብሎየተመሰከረላቸው መልካም ዛፎች ነበሩና:: መልካም ፍሬ ቅዱስ ዮሐንስን
አስገኙልን:: /ሉቃ.1፥6/:: ቅድስናቸው ከፍሬያቸው ከዮሐንስ የተነሳ ገኖ ዛሬም ድረስ ይታያል:: ለብዙዎች የሚሆን ደስታን
ወልደዋልና ስሙን ዮሐንስ አሉት ትርጓሜው ደስታ ማለት ነው:: የክርስቲያናዊ ጋብቻ ዓላማ ምእመናንን መልካም ዛፍ አድርጎ
መትከል ነው:: ሲንከባከቡትም እንደ ካህኑ ዘካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥ ደስታው ከቤተ ዘመድ ያለፈ መልካም ፍሬ ያፈራል::
በመጥምቁ ዮሐንስ ልደት “እነሆ፥ መልእክተኛዬን እልካለሁ፥ መንገድንም በፊቴ ያስተካክላል . . . ” በማለት ነቢያተ እግዚአብሔር
የተናገሩትን የትንቢት ቃል ለሚጠባበቁ ሁሉ ደስታ ነበረ:: /ሚል.3፥1 ፤ኢሳ.40፥3 ፤ማር.1፥1-5/:: የዮሐንስ መምጣት
ለጌታችን መምጣት የምሥራች ነውና:: “ከእኔ የሚበረታ በኋላዬ ይመጣል።” የሚለው ስብከቱም የሚያስታውሰን ይህንኑ ነው:: /
ማር.1፥7/:: በዮሐንስ መጥምቅ ልደት ደስ የሚሰኘው ያለፈውም የሚመጣውም ትውልድ ነው::
በዘመኑ የነበሩትን በትምህርቱ ደስ አስኝቷቸዋል:: ትምህርቱና ተግሣጹን የሰሙትን ከስህተት መልሷቸዋልና ደስ ተሰኝተውበታል::
በኃጢአት ያደፈ ስውነታቸውን በንስሀ ጥምቀት አዘጋጅቷልና ደስ ተሰኝተውበታል:: አገልግሎቱን በሚገባ የተረዳ መናኒ ነበርና
ሕይወቱ ደስ የሚያሰኝ ነበረ:: አገልግሎቱን የምታውቅ፥ ክብሩን የምትመሰክር፥ በቃል ኪዳኑ የምትታመን ቤተ ክርስቲያንም ደስ
ትስኝበታለች:: ስለዚህም በልደቱም በእረፍቱም ቀን የደስታ በዓል ታደርጋለች:: ምእመናንም በቃል ኪዳኑ በመታመን የምናደርገው
የመታሰቢያ በዓሉ ደስታን የሚሰጥ ነው:: በመወለዱ ያገኘናቸውን የመጥምቁን በረከቶች እያሰብን አምላኩን እናመሰግናለን:: ልደተ
ቅዱሳንን የማዘከር ዓላማው የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ አስቦ ለማመስገን ነው:: ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ልደት ስንናገር ወላጆቹንና
ጽድቃቸውን የአባቱን የክህነት አገልግሎት፥ የመልአኩን ተራዳኢነት፥ የእናቱን በመንፈስ ቅዱስ መቃኘት፥ የእርሱን በማኅጸን
መዝለል፥ የአባቱን አንደበት መክፈቱን፥ ስለ አደገበት የናዝራውያን ሥርዓት፥ ስለ አሳደገችው የበረሀ ፍየል /ቶራ/፥ ይመገበው
ስለነበረው አንበጣና የበረሀ ማር፥ ዞሮ ያስተማራቸው ትምህርቶች፥ ስለ ፈጸማቸው የጽድቅ ሥራዎች፥ ጌታችንን ስለ ማጥመቁ፥ ስለ
ተግሣጹና በሰማእትነት ስለ ማረፉ፥ ስለ ተዓምራቱ ከዚያም በኋላ በጸሎቱና በአማላጅነቱ ለሰው ልጆች ስለ ረዳው ርዳታ . . .
በደስታ በማውሳት ነው:: የሌሎችም ቅዱሳንን በዓል የምናከብረው በዚህ መንገድ ነው::
እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው:: ቅድስት ኤልሳቤጥን የጎበኛት ድንቅ ነው፤ የአገልጋዩን ድካም ያልዘነጋ ድንቅ ነው፤ ዘመን
ካለፋቸው በኋላ በእርግና ዘመናቸው ዘር የሰጠ ድንቅ ነው እያልን ደስ ተሰኝተን የምናመሰግነው በቅዱሳኑ ላይ ድንቅን ያደረገውን
እግዚአብሔርን ነው::/መዝ.68፥35/ “ከእናንተ መከራን የሚቀበል ማንም ቢኖር እርሱ ይጸልይ፤ ደስ የሚለውም ማንም ቢኖር
እርሱ ይዘምር።” ተብሏልና:: /ያዕ.5፥13/:: ልደተ ቅዱሳን የደስታ የዝማሬ በዓላት ናቸው:: የእግዚአብሔር ወዳጆች ቅዱሳን
ጽናታቸው ይደነቅበታል፥ አምላካቸው ይመሰገንበታል፥ ትምህርታቸው ይነገርበታል:: ስለ ቅዱሳን በመናገር የሚጠፋ ጊዜ የለም ፤
ስለ ቅዱሳን መመስከርን አብነት የምናደርገው መጽሐፍ ቅዱስን ነው:: መጽሐፍ ቅዱስን እናውቃለን ለሚሉን በውስጡ የበርካታ
ቅዱሳንን ልደት፥ እድገት፥ አገልግሎት፥ ትምህርት፥ ክብርና ጸጋ የሚመሰክር መጽሐፍ መሆኑን እንመሰክርላቸዋለን::
የመጥምቁ ዮሐንስ ልደት በዜማ በግጥም በንባብም ቢሆን የምናወሳው መጽሐፍ የመሰከረለትን እውነት ነው:: መጥምቁ ዮሐንስ
በመጽሐፍ ቅዱስ ነቢያት በትንቢት ቃል “የአዋጅ ነጋሪው ቃል” ፤“የቃል ኪዳን መልእክተኛ”፤ “መንገድ ጠራጊ”፤ “በበረሃ የሚጮኽ
ሰው ድምጽ” ወዘተ እያሉ አመስግነውታል:: መልአከ እግዚአብሔር ቅድስናውንና ክብሩን ሲናገር “ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ
ቅዱስ ይሞላበታል፤” ፥“ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል።” ብሎለታል ፤ ካህኑ ዘካርያስም በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ “አንተ
ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤” እያለ አገልግሎቱን ገልጧል ፤ ጌታችንም “እርሱ
የሚነድና የሚያበራ መብራት ነበረ፥” ፤ “እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ
አልተነሣም፤” ብሎ ሰማያዊ ክብሩን ገልጾለታል:: /ማቴ.11:11፤ ዮሐ.5፥35/:: ይገስጸው የነበረው ሄሮድስ እንኳን ሳይቀር
“ዮሐንስ ጻድቅና ቅዱስ ሰው እንደ ሆነ አውቆ ይፈራውና ይጠባበቀው ነበር፤ እርሱንም ሰምቶ በብዙ ነገር ያመነታ ነበር፤” ተብሎ
ተጽፏል:: /ማር.6፥20/:: የቅዱሳንን ሕይወት ማውሳት መጽሐፋዊ ነው፤ የምንለው በዚህ መንገድ ክብራቸውን፥
አገልግሎታቸውን፥ ቅድስናቸውን የምንመሰክር በመሆኑ ነው::
ቅዱስ ዮሐንስ ኤልያስን ይመስል የነበረ ነቢይ ነው:: ዮሐንስ መጥምቅና ነቢዩ ኤልያስ አኗኗራቸው ለመናንያን አርአያ ምሳሌ የሚሆን
ነበር:: ኤልያስ በበረሀ ኖሯል፥ ዮሐንስም እንደዚያው:: መምህራን ሲጠሯቸው መምህር ወመገስጽ ይሏቸዋል ኤልያስ አክአብን
ኤልዛቤልን ገስጿል፥ ዮሐንስም ሄሮድስን ገስጿል:: የጽድቅ ምስክሮች ነበሩ ኤልያስ ስለ ናቡቴ፥ ዮሐንስ ስለ ሕገ እግዚአብሔር
ተሟግተዋል:: ሌሎችም በርካታ ተመሳስሎ አላቸው፡፡ የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስን የልደቱን ዜና የተናገረው መልአክ
“በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል።” በማለት መሰከረለት:: /ሉቃ.1፥17/:: በነቢዩ ኤልያስ በቅዱስ ዮሐንስ መንገድ ሂደው
ያገለገሉ መናንያንን ሰማእታትን ስውራንን ቅዱሳንን ሁሉ እነርሱን እንዳከበርን እናከብራቸዋለን:: ገድላቸውን ጽፈን ተዓምራቸውን
ተናግረን ምስክርነታቸውን አጽንተን እንይዛለን:: የሕይወታቸውን የቃላቸውን የጽሑፋቸውን ትምህርት እንመሰክራለን:: ሕዝብ
ደስ እንዲለው:: ለሕገ እግዚአብሔር የሚቀኑ ስለ ደሀ መበደል ስለ ፍርድ መጓደል የሚታገሉ ጻድቃን ይበዙ ዘንድ በኤልያስ መንፈስ
በዮሐንስም መንገድ የሚመጡ ጻድቃን ለማፍራት ይረዳልና::/ምሳ.29፥2/::
የቅዱሳንን በዓል ማክበር የሚጠቅመው በረከታቸውን ለማግኘት ብቻ ሳይሆን የቅዱሳኑን ትምህርት ለመያዝም ነው:: በዓለ ቅዱሳን
ሲከበር ትምህርታቸውም ይዘከራል:: የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ትምህርቶች በአራቱም ወንጌላውያን ተዳሰዋል:: የመጥምቁ ታላላቅ
ትምህርቶች በሁለት ርእሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ነበሩ:: የመጀመሪያ ትምህርቱ የንስሐ ጥሪ ነው:: ሕዝቡ እንዲመለሱ ይሰብካል ፥
ደንዳና ልብ የነበራቸውን እንደ ሄሮድስና የአይሁድ መምህራን ያሉትን ይገስጻል:: ይህ ትምህርቱ ዘመኑን እየዋጀ በየዘመናቱ የሚነሱ
ምእመናንን ሕይወት ለማነጽ ይጠቅማል:: ወደ ቅዱስ ዮሐንስ ለመጡ ለሕዝቡ ቸርነትን ስለ ማድረግ፥ ለቀራጮች ስለ እውነት
ሚዛን፥ ለጭፍሮች ስለ ፍትሕ፥ . . . ያስተማራቸው ትምህርቶች ዘመናትን እየተሻገሩ የሚመክሩ ሁለት አፍ ያለው ሰይፍ ናቸው::/
ሉቃ.3፥11-14/:: የንስሐ ትምህርት ተግሣጽና ምክር ይሰጣል:: ከመጥምቀ መለኮት ከቅዱስ ዮሐንስ ትምህርት የተወሰደ ነው::
በዚህምክንያት ነው በዓለ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠናባቸው፥ የሚነገርባቸው፥ የሚተረጎምባቸው
ናቸው የምንለው::
ሁለተኛ ነገረ ሥጋዌ ላይ ያተኮረው ትምህርቱ ነው:: መጥምቁ ዮሐንስ የአምላክ ሰው የመሆን ምስጢርን ሲያስረዳ መሲህ ይመጣል
ተብሎ በነቢያት የተነገረው በጌታችን መፈጸሙን አስረግጦ የተናገረ መምህር ነው::/ዮሐ.1፥29-36/:: የዓለም መድኃኒት መሆኑንም
ከመልአኩ ቀጥሎ የመሰከረ ነቢይ ነው:: “የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።” ብሎታልና:: በሥጋ ልደት
ቢቀድመውም ለመለኮት ዘመን አይቆጠርለትምና ቅድመ ዓለም የነበረ ሕልውናውን “ከእኔም በፊት ነበር” ሲልም መስክሯል::
የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅን ምስክርነት ልዩ የሚያደርገው ነገርም አለ:: ምስክርነቱ የእውቀት ብቻ አይደለም:: በዮርዳኖስ ባሕር ቆሞ
ጌታውን ሲያጠምቅ ሰማይ ተከፍቶ ያየ የእግዚአብሔር አብን ምስክርነት የሰማ የምስጢር ሰው ነው:: አይሁድን ያሳፈረበት ትልቁ
ምስክርነቱም “እኔም አይቻለሁ እርሱም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ መስክሬአለሁ።” የሚለው ነው:: የነገረ ሥጋዌ ትምህርቱን
ሲደመድም “በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ
ሕይወትን አያይም።” ሲል የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን በሚገባ አስረድቷል:: /ዮሐ.3፥25-36/:: ጌታችንም የምስክርነቱን
እውነትነት “እናንተ ወደ ዮሐንስ ልካችኋል እርሱም ለእውነት መስክሮአል።” በማለት ገልጿል:: /ዮሐ.5፥33/:: በዓለ ቅዱሳን
በጠቅላላ ነገረ እግዚአብሔር የሚነገርባቸው፥ ትምህርተ ሃይማኖት የምናጠናባቸው፥ ታሪከ ቤተ ክርስቲያን የሚዘከርባቸው በዓላት
ናቸው::
በአጠቃላይ በዓለ ቅዱሳንን አታክብሩ ማለትን የሚያህል የወንጌል እንቅፋትነት የለም:: ጌታችን ባለሽቱዋ ማርያም በንስሐ እንባ
አጥባ ሽቱ ቀብታ መልካም አድርጋለችና ለውለታዋ መታሰቢያ ሲያቆም “እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ
በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል።” ካለ:: /ማቴ.26፥13/:: ስለ
ስሙ እስከ ሞት ድረስ ለተደበደቡ፥መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ፥ በእስራትና በወኅኒ ለተፈትኑ፥ በደንጊያ ተወግረው ለሞቱ፥ በመጋዝ
ለተሰነጠቁ፥ ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ለተቅበዘበዙ . . . ወዳጆቹማ እንዴት ያለ
መታሰቢያን ይሰጣቸው? የወንጌል ትምህርት ለሚተረጎምባቸው አብነቶችማ እንዴት አብልጦ አይሰጣቸውም?
በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በዓለ ቅዱሳን ሥርዓታዊና ትውፊታዊ በሆኑ መንገዶችም ይዘከራሉ:: ሥርዓታዊው መንገድ ገድልና
ተዓምር መጻፍ፥ ድርሳንና መልክ መድረስ፥ በስማቸው መቅደስ መሰየም፥ . . . ናቸው:: ትውፊታዊውም “ማንም ከእነዚህ
ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።” ከሚለው
አማናዊ ቃል ኪዳን ለመሳተፍ በቅዱሳኑ ስም ጸበል ጸዲቅ ማድረግን የመሰሉ ናቸው:: በመጥምቁ ዮሐንስ ስም የሚሰበሰቡ
ወዳጆቹም ገድሉን አንብበው፥ ተዓምሩን ተናግረው፥ ለነዳያን መጽውተው፥ ሰማእቱን ያዘክራሉ:: በልደቱ የወላጆቹን ሐዘን ያራቀ
በምልጃው ለሚተማመኑ መታሰቢያውን ለሚያደርጉ ወዳጆቹም ደዌያቸውን እያራቀ መንፈሳዊ ደስታን ያለብሳቸዋል::
የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ የልደቱ ረድኤትና በረከት አይለየን:
በዘሚካኤል አራንሺ
በዮሴፍ ወልደ ያዕቆብ ዘመን የነበረው ፈርኦንና የመጥምቁ ዮሐንስን አንገት ለዘፋኝ ወሮታ የሰጠው ሄሮድስ የሚያመሳስላቸው አንድ
ዓይነት ተግባር ፈጽመዋል:: ይኽውም ሁለቱም ልደታቸውን ያከብሩ እንደነበር በመጽሐፍ ቅዱስ መጠቀሱ ነው:: /ዘፍ.40፥20 ፤
ማቴ.14፥6/:: ታሪካቸውን ስናጠና ደግሞ በርካታ መመሳሰል እንደነበራቸው እንገነዘባለን:: ሁለቱም ነገሥታት ናቸው:: ሁለቱም
ንጹሐንን አስረዋል:: ሁለቱም ደም አፍሳሾች ነበሩ:: በልደት በዓላቸውም ነፍስ አጥፍተዋል:: በልደት በዓላቸው ነፍስ ያጠፉ
ሰዎች ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ መጻፉ የልደት በዓል ማክበርን ስህተት አያደርገውም:: በጌታችን ልደት መቶ አርባ አራት ሺህ
ሕጻናት በሄሮድስ ትእዛዝ ተገድለዋል:: የጌታችንን ልደት ግን እናከብራለን:: መግደል ኃጢአት መሆኑን እንመሰክርበት ካልሆነ በቀር
ነፍስ በማጥፋት የሚከበር በዓል የለንም:: የፋሲካን በዓል በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ለማክበር እንገደዳለን እንጂ ዘፋኞች ድግስ
ስለሚያዘጋጁበት ማክበሩ ቢቀር ቢባል ሞኝነት ነው:: ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን የቅዱሳንን ልደት በዓል ስታከብር የራሷ
ሥርዓትና ባሕል የበዓላት መቁጠሪያ /ሊተርጂካል ካላንደር/ አላት:: የቱ መቼ መከበር እንዳለበትም ምክንያታዊ በሆነ መንገድ
ታስረዳለች:: ጥንታዊት ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆንዋም በርግጥኝነት ዕለታቱን ቆጥራ ትናገራለች:: በነቢይ የአዋጅ ነጋሪ
ቃል ተብሎ የተነገረለት የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስን የልደት በዓል የምታከብረው በሰኔ ሠላሳ ቀን ነው::
የጻድቃን ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ እንደሆነ፤ ቅዱሳኑን ያገኘንባት ልደታቸውም የከበረች ናት:: /መዝ.116፥15/::
የመጥምቁ ዮሐንስን ልደት ያበሰረው መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል “በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል::” እንዳለ በልደተ ቅዱሳን ደስ
እንሰኛለን:: /ሉቃ.1፥14/:: በዓለ ቅዱሳን የደስታ በዓላት ናቸውና:: የተወለዱበት ፥ ልዩ ልዩ ገቢረ ተዓምራት ወመንክራት
የፈጸሙባቸው፥ ሰማእተ ኢየሱስ ሆነው መከራ የተቀበሉባቸው፥ያረፉበትና የተሰወሩበት፥ ቃል ኪዳን የተቀበሉባቸውን ዕለታት
የምናከብረው በደስታ ነው:: ቅዱስ ዳዊት “ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ምስጋና መኖሪያ ስፍራ እገባለሁና በዓል የሚያደርጉ ሰዎች
የደስታና ምስጋና ቃል አሰሙ።” እንዲል:: /መዝ.42፥4/:: ዕለታቱ በደንጊያ ተወግረው፥ በመጋዝ ተተርትረው ፥ ወደ እሳት
ተጥለው፥ ለአናብስት ተሰጥተው፥ በሰማእትነት ያረፉባቸው እንኳ ቢሆኑ የደስታ በዓላት ናቸው:: የምስክርነታቸውን እውነትነት፥
የእምነታቸውን ጽናት፥ ታዛዥነታቸውንና ለአምላካቸው ያላቸውን ፍቅር በመግለጣቸው፤ የሚያገኙትን ክብር፥ የሚወርሱትን
መንግስት እናስባለንና:: የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅን የከበረች የእረፍቱን ቀን በማኅሌት ከበሮ መትተን፥ጸናጽል ጸንጽለን፥ ወረብ
ወርበን፥ ቅዳሴ ቀድሰን፥ መዝሙር ዘምረን፥ መልክ ደግመን፥ ገድል አንብበን፥ ተዓምሩን ተናግረን፥ ቅድስናውን መስክረን
እንደምናከብረው በዓለ ልደቱንም እንዲሁ እናከብራለን:: ጠቢቡ “ጻድቃን በበዙ ጊዜ ሕዝብ ደስ ይለዋል...” ብሏልና::
በመወለዳቸው ደስ ተሰኝተን በዓል እናደርጋለን:: /ምሳ.29፥2/::ካህኑ ዘካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥ የብዙዎችን ደስታ ወልደዋል::
ጌታችን በወንጌል “መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፥ . . . ” /ማቴ.7፥17-19/:: በማለት እንዳስተማረን የመጥምቁ
ወላጆች “በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ” ተብሎየተመሰከረላቸው መልካም ዛፎች ነበሩና:: መልካም ፍሬ ቅዱስ ዮሐንስን
አስገኙልን:: /ሉቃ.1፥6/:: ቅድስናቸው ከፍሬያቸው ከዮሐንስ የተነሳ ገኖ ዛሬም ድረስ ይታያል:: ለብዙዎች የሚሆን ደስታን
ወልደዋልና ስሙን ዮሐንስ አሉት ትርጓሜው ደስታ ማለት ነው:: የክርስቲያናዊ ጋብቻ ዓላማ ምእመናንን መልካም ዛፍ አድርጎ
መትከል ነው:: ሲንከባከቡትም እንደ ካህኑ ዘካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥ ደስታው ከቤተ ዘመድ ያለፈ መልካም ፍሬ ያፈራል::
በመጥምቁ ዮሐንስ ልደት “እነሆ፥ መልእክተኛዬን እልካለሁ፥ መንገድንም በፊቴ ያስተካክላል . . . ” በማለት ነቢያተ እግዚአብሔር
የተናገሩትን የትንቢት ቃል ለሚጠባበቁ ሁሉ ደስታ ነበረ:: /ሚል.3፥1 ፤ኢሳ.40፥3 ፤ማር.1፥1-5/:: የዮሐንስ መምጣት
ለጌታችን መምጣት የምሥራች ነውና:: “ከእኔ የሚበረታ በኋላዬ ይመጣል።” የሚለው ስብከቱም የሚያስታውሰን ይህንኑ ነው:: /
ማር.1፥7/:: በዮሐንስ መጥምቅ ልደት ደስ የሚሰኘው ያለፈውም የሚመጣውም ትውልድ ነው::
በዘመኑ የነበሩትን በትምህርቱ ደስ አስኝቷቸዋል:: ትምህርቱና ተግሣጹን የሰሙትን ከስህተት መልሷቸዋልና ደስ ተሰኝተውበታል::
በኃጢአት ያደፈ ስውነታቸውን በንስሀ ጥምቀት አዘጋጅቷልና ደስ ተሰኝተውበታል:: አገልግሎቱን በሚገባ የተረዳ መናኒ ነበርና
ሕይወቱ ደስ የሚያሰኝ ነበረ:: አገልግሎቱን የምታውቅ፥ ክብሩን የምትመሰክር፥ በቃል ኪዳኑ የምትታመን ቤተ ክርስቲያንም ደስ
ትስኝበታለች:: ስለዚህም በልደቱም በእረፍቱም ቀን የደስታ በዓል ታደርጋለች:: ምእመናንም በቃል ኪዳኑ በመታመን የምናደርገው
የመታሰቢያ በዓሉ ደስታን የሚሰጥ ነው:: በመወለዱ ያገኘናቸውን የመጥምቁን በረከቶች እያሰብን አምላኩን እናመሰግናለን:: ልደተ
ቅዱሳንን የማዘከር ዓላማው የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ አስቦ ለማመስገን ነው:: ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ልደት ስንናገር ወላጆቹንና
ጽድቃቸውን የአባቱን የክህነት አገልግሎት፥ የመልአኩን ተራዳኢነት፥ የእናቱን በመንፈስ ቅዱስ መቃኘት፥ የእርሱን በማኅጸን
መዝለል፥ የአባቱን አንደበት መክፈቱን፥ ስለ አደገበት የናዝራውያን ሥርዓት፥ ስለ አሳደገችው የበረሀ ፍየል /ቶራ/፥ ይመገበው
ስለነበረው አንበጣና የበረሀ ማር፥ ዞሮ ያስተማራቸው ትምህርቶች፥ ስለ ፈጸማቸው የጽድቅ ሥራዎች፥ ጌታችንን ስለ ማጥመቁ፥ ስለ
ተግሣጹና በሰማእትነት ስለ ማረፉ፥ ስለ ተዓምራቱ ከዚያም በኋላ በጸሎቱና በአማላጅነቱ ለሰው ልጆች ስለ ረዳው ርዳታ . . .
በደስታ በማውሳት ነው:: የሌሎችም ቅዱሳንን በዓል የምናከብረው በዚህ መንገድ ነው::
እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው:: ቅድስት ኤልሳቤጥን የጎበኛት ድንቅ ነው፤ የአገልጋዩን ድካም ያልዘነጋ ድንቅ ነው፤ ዘመን
ካለፋቸው በኋላ በእርግና ዘመናቸው ዘር የሰጠ ድንቅ ነው እያልን ደስ ተሰኝተን የምናመሰግነው በቅዱሳኑ ላይ ድንቅን ያደረገውን
እግዚአብሔርን ነው::/መዝ.68፥35/ “ከእናንተ መከራን የሚቀበል ማንም ቢኖር እርሱ ይጸልይ፤ ደስ የሚለውም ማንም ቢኖር
እርሱ ይዘምር።” ተብሏልና:: /ያዕ.5፥13/:: ልደተ ቅዱሳን የደስታ የዝማሬ በዓላት ናቸው:: የእግዚአብሔር ወዳጆች ቅዱሳን
ጽናታቸው ይደነቅበታል፥ አምላካቸው ይመሰገንበታል፥ ትምህርታቸው ይነገርበታል:: ስለ ቅዱሳን በመናገር የሚጠፋ ጊዜ የለም ፤
ስለ ቅዱሳን መመስከርን አብነት የምናደርገው መጽሐፍ ቅዱስን ነው:: መጽሐፍ ቅዱስን እናውቃለን ለሚሉን በውስጡ የበርካታ
ቅዱሳንን ልደት፥ እድገት፥ አገልግሎት፥ ትምህርት፥ ክብርና ጸጋ የሚመሰክር መጽሐፍ መሆኑን እንመሰክርላቸዋለን::
የመጥምቁ ዮሐንስ ልደት በዜማ በግጥም በንባብም ቢሆን የምናወሳው መጽሐፍ የመሰከረለትን እውነት ነው:: መጥምቁ ዮሐንስ
በመጽሐፍ ቅዱስ ነቢያት በትንቢት ቃል “የአዋጅ ነጋሪው ቃል” ፤“የቃል ኪዳን መልእክተኛ”፤ “መንገድ ጠራጊ”፤ “በበረሃ የሚጮኽ
ሰው ድምጽ” ወዘተ እያሉ አመስግነውታል:: መልአከ እግዚአብሔር ቅድስናውንና ክብሩን ሲናገር “ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ
ቅዱስ ይሞላበታል፤” ፥“ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል።” ብሎለታል ፤ ካህኑ ዘካርያስም በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ “አንተ
ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤” እያለ አገልግሎቱን ገልጧል ፤ ጌታችንም “እርሱ
የሚነድና የሚያበራ መብራት ነበረ፥” ፤ “እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ
አልተነሣም፤” ብሎ ሰማያዊ ክብሩን ገልጾለታል:: /ማቴ.11:11፤ ዮሐ.5፥35/:: ይገስጸው የነበረው ሄሮድስ እንኳን ሳይቀር
“ዮሐንስ ጻድቅና ቅዱስ ሰው እንደ ሆነ አውቆ ይፈራውና ይጠባበቀው ነበር፤ እርሱንም ሰምቶ በብዙ ነገር ያመነታ ነበር፤” ተብሎ
ተጽፏል:: /ማር.6፥20/:: የቅዱሳንን ሕይወት ማውሳት መጽሐፋዊ ነው፤ የምንለው በዚህ መንገድ ክብራቸውን፥
አገልግሎታቸውን፥ ቅድስናቸውን የምንመሰክር በመሆኑ ነው::
ቅዱስ ዮሐንስ ኤልያስን ይመስል የነበረ ነቢይ ነው:: ዮሐንስ መጥምቅና ነቢዩ ኤልያስ አኗኗራቸው ለመናንያን አርአያ ምሳሌ የሚሆን
ነበር:: ኤልያስ በበረሀ ኖሯል፥ ዮሐንስም እንደዚያው:: መምህራን ሲጠሯቸው መምህር ወመገስጽ ይሏቸዋል ኤልያስ አክአብን
ኤልዛቤልን ገስጿል፥ ዮሐንስም ሄሮድስን ገስጿል:: የጽድቅ ምስክሮች ነበሩ ኤልያስ ስለ ናቡቴ፥ ዮሐንስ ስለ ሕገ እግዚአብሔር
ተሟግተዋል:: ሌሎችም በርካታ ተመሳስሎ አላቸው፡፡ የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስን የልደቱን ዜና የተናገረው መልአክ
“በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል።” በማለት መሰከረለት:: /ሉቃ.1፥17/:: በነቢዩ ኤልያስ በቅዱስ ዮሐንስ መንገድ ሂደው
ያገለገሉ መናንያንን ሰማእታትን ስውራንን ቅዱሳንን ሁሉ እነርሱን እንዳከበርን እናከብራቸዋለን:: ገድላቸውን ጽፈን ተዓምራቸውን
ተናግረን ምስክርነታቸውን አጽንተን እንይዛለን:: የሕይወታቸውን የቃላቸውን የጽሑፋቸውን ትምህርት እንመሰክራለን:: ሕዝብ
ደስ እንዲለው:: ለሕገ እግዚአብሔር የሚቀኑ ስለ ደሀ መበደል ስለ ፍርድ መጓደል የሚታገሉ ጻድቃን ይበዙ ዘንድ በኤልያስ መንፈስ
በዮሐንስም መንገድ የሚመጡ ጻድቃን ለማፍራት ይረዳልና::/ምሳ.29፥2/::
የቅዱሳንን በዓል ማክበር የሚጠቅመው በረከታቸውን ለማግኘት ብቻ ሳይሆን የቅዱሳኑን ትምህርት ለመያዝም ነው:: በዓለ ቅዱሳን
ሲከበር ትምህርታቸውም ይዘከራል:: የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ትምህርቶች በአራቱም ወንጌላውያን ተዳሰዋል:: የመጥምቁ ታላላቅ
ትምህርቶች በሁለት ርእሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ነበሩ:: የመጀመሪያ ትምህርቱ የንስሐ ጥሪ ነው:: ሕዝቡ እንዲመለሱ ይሰብካል ፥
ደንዳና ልብ የነበራቸውን እንደ ሄሮድስና የአይሁድ መምህራን ያሉትን ይገስጻል:: ይህ ትምህርቱ ዘመኑን እየዋጀ በየዘመናቱ የሚነሱ
ምእመናንን ሕይወት ለማነጽ ይጠቅማል:: ወደ ቅዱስ ዮሐንስ ለመጡ ለሕዝቡ ቸርነትን ስለ ማድረግ፥ ለቀራጮች ስለ እውነት
ሚዛን፥ ለጭፍሮች ስለ ፍትሕ፥ . . . ያስተማራቸው ትምህርቶች ዘመናትን እየተሻገሩ የሚመክሩ ሁለት አፍ ያለው ሰይፍ ናቸው::/
ሉቃ.3፥11-14/:: የንስሐ ትምህርት ተግሣጽና ምክር ይሰጣል:: ከመጥምቀ መለኮት ከቅዱስ ዮሐንስ ትምህርት የተወሰደ ነው::
በዚህምክንያት ነው በዓለ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠናባቸው፥ የሚነገርባቸው፥ የሚተረጎምባቸው
ናቸው የምንለው::
ሁለተኛ ነገረ ሥጋዌ ላይ ያተኮረው ትምህርቱ ነው:: መጥምቁ ዮሐንስ የአምላክ ሰው የመሆን ምስጢርን ሲያስረዳ መሲህ ይመጣል
ተብሎ በነቢያት የተነገረው በጌታችን መፈጸሙን አስረግጦ የተናገረ መምህር ነው::/ዮሐ.1፥29-36/:: የዓለም መድኃኒት መሆኑንም
ከመልአኩ ቀጥሎ የመሰከረ ነቢይ ነው:: “የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።” ብሎታልና:: በሥጋ ልደት
ቢቀድመውም ለመለኮት ዘመን አይቆጠርለትምና ቅድመ ዓለም የነበረ ሕልውናውን “ከእኔም በፊት ነበር” ሲልም መስክሯል::
የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅን ምስክርነት ልዩ የሚያደርገው ነገርም አለ:: ምስክርነቱ የእውቀት ብቻ አይደለም:: በዮርዳኖስ ባሕር ቆሞ
ጌታውን ሲያጠምቅ ሰማይ ተከፍቶ ያየ የእግዚአብሔር አብን ምስክርነት የሰማ የምስጢር ሰው ነው:: አይሁድን ያሳፈረበት ትልቁ
ምስክርነቱም “እኔም አይቻለሁ እርሱም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ መስክሬአለሁ።” የሚለው ነው:: የነገረ ሥጋዌ ትምህርቱን
ሲደመድም “በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ
ሕይወትን አያይም።” ሲል የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን በሚገባ አስረድቷል:: /ዮሐ.3፥25-36/:: ጌታችንም የምስክርነቱን
እውነትነት “እናንተ ወደ ዮሐንስ ልካችኋል እርሱም ለእውነት መስክሮአል።” በማለት ገልጿል:: /ዮሐ.5፥33/:: በዓለ ቅዱሳን
በጠቅላላ ነገረ እግዚአብሔር የሚነገርባቸው፥ ትምህርተ ሃይማኖት የምናጠናባቸው፥ ታሪከ ቤተ ክርስቲያን የሚዘከርባቸው በዓላት
ናቸው::
በአጠቃላይ በዓለ ቅዱሳንን አታክብሩ ማለትን የሚያህል የወንጌል እንቅፋትነት የለም:: ጌታችን ባለሽቱዋ ማርያም በንስሐ እንባ
አጥባ ሽቱ ቀብታ መልካም አድርጋለችና ለውለታዋ መታሰቢያ ሲያቆም “እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ
በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል።” ካለ:: /ማቴ.26፥13/:: ስለ
ስሙ እስከ ሞት ድረስ ለተደበደቡ፥መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ፥ በእስራትና በወኅኒ ለተፈትኑ፥ በደንጊያ ተወግረው ለሞቱ፥ በመጋዝ
ለተሰነጠቁ፥ ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ለተቅበዘበዙ . . . ወዳጆቹማ እንዴት ያለ
መታሰቢያን ይሰጣቸው? የወንጌል ትምህርት ለሚተረጎምባቸው አብነቶችማ እንዴት አብልጦ አይሰጣቸውም?
በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በዓለ ቅዱሳን ሥርዓታዊና ትውፊታዊ በሆኑ መንገዶችም ይዘከራሉ:: ሥርዓታዊው መንገድ ገድልና
ተዓምር መጻፍ፥ ድርሳንና መልክ መድረስ፥ በስማቸው መቅደስ መሰየም፥ . . . ናቸው:: ትውፊታዊውም “ማንም ከእነዚህ
ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም።” ከሚለው
አማናዊ ቃል ኪዳን ለመሳተፍ በቅዱሳኑ ስም ጸበል ጸዲቅ ማድረግን የመሰሉ ናቸው:: በመጥምቁ ዮሐንስ ስም የሚሰበሰቡ
ወዳጆቹም ገድሉን አንብበው፥ ተዓምሩን ተናግረው፥ ለነዳያን መጽውተው፥ ሰማእቱን ያዘክራሉ:: በልደቱ የወላጆቹን ሐዘን ያራቀ
በምልጃው ለሚተማመኑ መታሰቢያውን ለሚያደርጉ ወዳጆቹም ደዌያቸውን እያራቀ መንፈሳዊ ደስታን ያለብሳቸዋል::
የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ የልደቱ ረድኤትና በረከት አይለየን:

27 comments:
One day a courageous man shold do this.
ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባበራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፥10
መለያየትን የሚያነሣ ሰው ጠማማ እንዲሆን በራሱም ላይ ፈርዶ ኃጢአትን እንዲያደርግ አውቀህ፥ አንድ ጊዜ ሁለት ጊዜም ከገሠጽኸው በኋላ እንዲህ ከሚመስል ሰው ራቅ።
ወደ ቲቶ 3 10፥11
ይህንም እላለሁ። እያንዳንዳችሁ። እኔ የጳውሎስ ነኝ፥ እኔስ የአጵሎስ ነኝ፥ እኔ ግን የኬፋ ነኝ፥ እኔስ የክርስቶስ ነኝ ትላላችሁ።
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፥12
ከላይ የቅዱሱን የእግዚአብሔር ቃል ለማስታወስ እንደሞከርኩት ቤተክርስቲያናችን የምትሰብከው እውነተኛው መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል እኛ ማን እንደሰበከንም ማወቅ የተሳነን ይመስለኛል እባካችሁ ሰዎችን አንመልከት በቃሉ ብቻ እንመራ ሰዎች በሚዘረጉት መንገድ አንጓዝ እግዚአብሔርን ብቻ እንከተል እውነቱ የት እንዳለ እያወቅን ለስጋዊ ጥቅምና ለዘረኝነት ቦታ አንስጥ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እንደሆነች ምንጊዜም ንጽህት ናት ብናጠፋ ብንበድል እራሳችን እንጠፋለን እንጅ ቤተክርስቲያንን አንጎዳትም ስለዚህ ለሰላምና ለይቅርታ ልባችንን እንክፈት የሰላም አምላክ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ይቅርታዉን እና ምህረቱን ያውርድልን ወስብሃት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመሰቀሉ ክቡር አሜን ,,,
You are a living evidence for the inevitable freedom of our beloved church from the tribal thugs, the day time robbers, the taxi driving and parking lot bandits, the ehapa derg & woyane murderers who have been hell bent all along to disrupt, weaken and control the church so that they can spearhead their futile political agenda which usually is designed to oppress the peace loving people and pillage the country Ethiopia. I was hoping that one day Mahiber Kidusan to liberate the church from the stranglehold of the poisonous and parasite Ethiopians, unfortunately it seems that the Mahiber is spineless, dangerous, wicked, and righteous all at once just like the Lucifer. Therefore, the key lies in the hands of independent minded Ethiopians, which i thing the editor/s of this blog sphere rightly represents. Please, use it wisely.
ገና ዛሬ ቁም ነገርና ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን የወገነ ሀሳብ ስታቀርብ አገኘኋት ::
የእኛ ችግራችን እኮ : ችግሩን በግልጽ እያወቅነው :
በቀጥታ ችግሩን ከመግለጽ ይልቅ : የራስን የቡድን ስሜት በሌላው ክፍል ላይ ለመጫን የሚደረገ ጨለምተኛነት ነው ::
እኔ ከምስማማባቸው ነጥቦች መካከል
1. በውስጥም በውጭም ያለችው ቤተ ክርስቲያናችን በፖለቲካኞች ስር መውደቋ
2. ይህን ክፍተት ተጠቅመው በውስጧ የተሰገሰጉት መናፍቃን እና ፀረ ቤተ ክርስቲያን/ሃይማኖት የሆነው አጥፊ ተግባራቸው ::
3. ዓላማ የሌላቸው እና ለጥቅማቸው ብቻ ያደሩ : ከዛም በላይ በአንድ እጃቸው መስቀል በሌላው እጃቸው የፖለቲካ መሳሪያ ያሆኑ : ካሕናት መበራከት ::
ሲሆኑ :
[u]ለዚህ ሁሉ ችግራችን መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስበው[/u]
በመጀመሪያ ደረጃ : በሁለቱ አባቶች (አቡነ መርቆሬዎስና ዐቡነ ጳውሎስ) እና በተከታዮቻቸው መካከል ያለው ቅራኔ የሚፈታበትን ሂደት ለማሳካት መረባረብ ::
ቤተ ክርስቲያኗ አንድ አስተዳደር መከተል ከጀመረች : ኃይሏን አሰባስባ :
. ከመንግስት ጣልቃ ገብንተ ራሷን ለመከላከልና
. በስጧ የተሰግሰጉ መናፍቅቃንን ነቅሶ ለማውጣት ትችላለች ::
ገና ዛሬ ቁም ነገርና ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን የወገነ ሀሳብ ስታቀርብ አገኘኋት ::
የእኛ ችግራችን እኮ : ችግሩን በግልጽ እያወቅነው :
በቀጥታ ችግሩን ከመግለጽ ይልቅ : የራስን የቡድን ስሜት በሌላው ክፍል ላይ ለመጫን የሚደረገ ጨለምተኛነት ነው ::
እኔ ከምስማማባቸው ነጥቦች መካከል
1. በውስጥም በውጭም ያለችው ቤተ ክርስቲያናችን በፖለቲካኞች ስር መውደቋ
2. ይህን ክፍተት ተጠቅመው በውስጧ የተሰገሰጉት መናፍቃን እና ፀረ ቤተ ክርስቲያን/ሃይማኖት የሆነው አጥፊ ተግባራቸው ::
3. ዓላማ የሌላቸው እና ለጥቅማቸው ብቻ ያደሩ : ከዛም በላይ በአንድ እጃቸው መስቀል በሌላው እጃቸው የፖለቲካ መሳሪያ ያሆኑ : ካሕናት መበራከት ::
ሲሆኑ :
[u]ለዚህ ሁሉ ችግራችን መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስበው[/u]
በመጀመሪያ ደረጃ : በሁለቱ አባቶች (አቡነ መርቆሬዎስና ዐቡነ ጳውሎስ) እና በተከታዮቻቸው መካከል ያለው ቅራኔ የሚፈታበትን ሂደት ለማሳካት መረባረብ ::
ቤተ ክርስቲያኗ አንድ አስተዳደር መከተል ከጀመረች : ኃይሏን አሰባስባ :
. ከመንግስት ጣልቃ ገብንተ ራሷን ለመከላከልና
. በስጧ የተሰግሰጉ መናፍቅቃንን ነቅሶ ለማውጣት ትችላለች ::
It is fantastic and very very true article.
- The 1960s generation is passing soon.Now stand the new generation with your new and energetic power.God will be with you.
- Learn from Abune Shinoda of Egypt coptic church.They were in the same problem some 10 years back.Now their church administrative and spritual problems are solved.Their only problem is extrem muslims attack.
- Both TERARA YANKETEKETE TIWLID and YA TIWLID actors shouldn't feel bad with the fact that is written here above.Becouse it is not difficult to think as if they did all just by thinking for their mother land-Ethiopia.But past exeperiance show us all failurity.So shoudl we continue in the same way? NO BIG NO!!!!!
- Pick up your visible and invisible hands from church.You will see all what you wish to see.Since all of us are under the hands of our Almight God, we all shall get our lessons according to our acts.
YE ABATOCHACHIN AMLAK YILEMENEN
AMEN
Atnatewos
one of the remedies for most of the problems in the Ethiopian orthodox tewahedo chruch here and in Ethiopia is the lack of unity among her followers of the faith.
We need ot bring our church fathers and resolve their differences. One hugh shortcoming of this DejeSelam is the absence of this topic in its leading article/postings. As is the case in past postings, this article does not put forth the need for the unity of church fathers. I know it is not be mistake and it bothers me.
My other comment is that, it is a known fact that Mahebere kedusan plays a big role in the shaping of the church's current conditions in Ethiopia and aboard. Most of the blame pointed at the others groups in the article can fairly be pointed at this group. The case in point is the situation at Dallas Kidus Mikael. MK needs to learn there is victory in loosing xsome battles. Bemeshenf Mashenef ...
I admit that politically-driven Ethiopian have heavely affect the dynamics of the chruch. However, there are those of us, who are not Woyane and are not old enough to have been in EPRP? We see what we do not like at church. We object many activities done in our chruches in the name of the church. We do not like ot see those who put their group's abjective before that of the church, including Mahebere Kidusan. We would like members of MK to take part in many church affairs, but we also want them to stop some the dominance they want ot have in many church affairs.
We are not Woyane, EPRP, or Menafikan ... Do not forget to include our concerns in the next parts of your article. I have a feeling anyone who even wants to give constructive feedback to members of the group is seen as opponent. So, surprise me by not labeling me and my kinds as Menafik and admit some of the mistakes, take responsibility and share that with us.
Stop and analyze your history once , let’s go back to the 3rd century ,we find great bishop and great kings.Abune selam and king St.Ezana & king St.Sizana , starting from them we have been using the political power for our church benefit. Even before that the Ethiopian jandereba went to Jerusalem why one of the reasons is he was government trader.
All our fathers prioritize their religion from their political stage. So They used it all. We are all very gready ,selfish, illiterate ,in love with abroad , hate each other….generally we all prioritize this world zan our spiritual life.
I sent a message for many peoples saying “ which party’s idea is good for our church?” No body cares or nobody wants to say it to me. One thing I was sure no body knew for sure. Let me tell u one thing z protestants are already competing in this election as a party . What exactly were u saying ,<< z politics should leave us alone.>> My brothers u are sleeping. wake up and start z rite politics ,otherwise the others will rotate us as they like. I hope u know where that takes church. And … I am sorry to say it but it is painful truth. There will be no Ethiopian orthodox church soon.
May God be with us all.
Stop and analyze your history once , let’s go back to the 3rd century ,we find great bishop and great kings.Abune selam and king St.Ezana & king St.Sizana , starting from them we have been using the political power for our church benefit. Even before that the Ethiopian jandereba went to Jerusalem why one of the reasons is he was government trader.
All our fathers prioritize their religion from their political stage. So They used it all. We are all very gready ,selfish, illiterate ,in love with abroad , hate each other….generally we all prioritize this world zan our spiritual life.
I sent a message for many peoples saying “ which party’s idea is good for our church?” No body cares or nobody wants to say it to me. One thing I was sure no body knew for sure. Let me tell u one thing z protestants are already competing in this election as a party . What exactly were u saying ,<< z politics should leave us alone.>> My brothers u are sleeping. wake up and start z rite politics ,otherwise the others will rotate us as they like. I hope u know where that takes church. And … I am sorry to say it but it is painful truth. There will be no Ethiopian orthodox church soon.
May God be with us all.
ይህን የመሰለ ያላዳላ ትክክለኛ ጽሑፍ ማቅረባችሁ ብእውነት በጣም እናመሰግናችሁ ኣለን።
እውነትና ግንባር ኣይሸሸግም እንደሚሉ ኣበው፡
ያቀረባችሁ ኣስተያየት በጣም የሚደገፍና ሁላችንም ልናስብበት የሚገባን ጉዳይ ነው።
ግን ኣንዴ ላስታውሳጭሁ።
ቤተ ክርስቲያናችን የውስጥ ምስጥ የሆንዋት፡ ፖለቲኮኞች ብጃ ኣይደሉም።
ኣቡነ ጳውሎስና ኣቡነ መርቆሬዎስም ለብቻቸው ኣይደሉም።
እውነቱን ማወቅና መድኃኒት ልንፈልግለት የሚገባን ጉዳይ የማህበረ ቅዱሳን ጉዳይ ነው።
ይህ ማኅበር፡ ለቤተ ክርስቲያናችን፡ በጣም ኣደገኛ ስብስብ ነው፡ በዚህ ኣደገና ድርጅት ያልተሰደበ ጳጳስ። ፓትርያርክ፡ ካህን፡ ዲያቆን፡ ወጣት ኣለ ለማለት የሚቻል ኣይመስለኝም፡ የእነሱን ሓሳብና መንገዲ ያልተቀበሉ ሁሉ፡ መናፍቅ፡ ከሓዲ፡ ኦርቶጰንጤ፡ ተሓድሶ፡ ወዘተ የሚል ጥላሸት በመቅባት ስምን በማጉደፍ፡ እንደ ተዋጊ ቀንዳም በሬ፡ ከቤተ ክርስቲያን ያባረርዋቸውና ያጠፍዋቸው ኣማንያን ስፍር ቁጥር የላቸውም።
ከመናፍቃን ጋር፡ ገዥና ሸያጭ የተስማሙ ነው የሚመስለውን፡
ቤተ ክርስቲያናችን ሰላምን እንድታገኝ፡ ይህ ማኅበር ኣካሄዱን ተመልሶ መገምገምና ማረብ ኣለበት ባይ ነኝ።
በደሙ የዋጃትን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይጠብቅ ኣምላክ። ኣሜን
may God give us our church chance to rise up again!
ለማነኛውም ስራቸውን ለማየት ስትሞክር እውነቱን ታገኛለህ::
እንዲየውም ጌታ እነሱን ባያስነሳ ኖሮ ዛሬ መናፍቅ ሀገሪቱን በተቆጣጠረ ነበር ::
እረ እንዲየዉም ያበርታቸው!
የቅዱሳን አምላክ እ/ር ለቤተክርስቲያናችን ሰው ይላክልን አሜን
Yes, we moderate comments to fence out unethical people who have no decency of matured dialogue. Since you are not using any name, we could not know if you have previously written us or not. Still, you blamed us to be partisan but not substantiate your comments with evidence. If you think our reports are not fair and true, then challenge us. By the way, Deje Selam will continue to write on Dallas case in depth, with the will of God. It is time to defend our Church; nothing but the Church, so help us God.
Cher Were Yaseman,
DS Team
በመጀመሪያ ደረጃ አባቶችን ታውቋቸዋላችሁ? በተለይ በኢትዮጵያ ያሉትን:: ልካችሁን ብታውቁ ጥሩ ነው ቢያንስ እዚህ ከምንጽፈው የሚበልጥ የአገልግሎትና የቅድስና ሕይወት አላቸው ሁላችሁም ይህን አታጡትም::ነገር ግን በድፍረት ለመሳደብ ትፈጥናላችሁ ጽድቅ በስድብ አይሰራም::
ezih ethiopia yaluten abatoch yetewesenutinim bihon awkachewalehu betikikil le K/BETEKRISTIYAN agelgilot yemifatenu nachew min albat egna yemanawkachew bizu negeroch sileminoru zim bilen negerochin bandefedifibachew melkam new elalehu.
yalutin chigiroch lemekref ende meftihe yemasibew
1. ezih blog lay asteyayet yeminisetim hone yeminaneb sewoch betikikil sile k/BETEKRISTIYan andinet kelib honen entseliy yetselotachinin waga GETA aynesanim ena
2. abatochin yeminikerb sewoch degmo yegil tikmachinin kemasaded yalutin chigiroch eske meftiheyachew bedenb discuss madreg. yihinin sil beteley huletuin kidusan abatochin yeminikerb sewoch(betsu'e wekidus Aba Paulosin ena Abune Merkoriyosin malete new).
3. kezih wichi K/Betkristiyanin lematfat yeminrwarwat sewoch degmo k/BETKRISTIYAN yetemeseretechiw BE KIRISTOS dem mehonun banzenega ena arfen quch binil degmo GETA lobona endiseten binteyikew. Keminim neger belay degmo melkam ayeseru yalu ye agelgilot mahiberatin yelele sim eyeseten yeminisadebewn binakom yetim silemanders.
4.be melkam agelgilot lay yalen degmo be agelgilotaachin yebelete binitega.
elalehu
Ye AMLAKACHIN cherinet ye EMEBETACHIN amalaginet ye KIDUSAN miljana tselot KIDIST BETEKRISTIYANIN and yadirgili
Amen
Abetu! yezelalem abat, yeselam aleka medihane-alem kiristos hoy, weden fekiden balametanew zer eyetemekan andituan b/k lemafires yeminitatarewin wede libonachin melisen! lemiyalefew lemitefaw poletica, siltan, lemayazalik sigawi tikim bilen zelalemawituan tewahido kebizu akitacha leminiwegat hulu akimachin min yahil endehone bemitasayibet menged tastemiren timekiren zend enimatsenihalen! Libonachinin bezer-manzer, befikre niway ena be-tihibit tebtibo ye-yazewin telat diabilosin, kefitretat hulu akibirehe bemeretikat beazagnitu enatachin dingil mariam lekso ena milja arikilin!. Yemininafikewin selam, fikir ena andinte be-betihe tatsena zend enileminihalen!!!
አቡነ ጳውሎስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መሪ ናቸው፤ የጻፉት መጽሐፍ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ዕምነትና ዶግማ ነውን?
አቶ ክፍሉ ታደሰ የኢሕአፓ አመራር አባል የነበሩ፤ [አሁን ግን እርሳቸው ይወቁት]፤ አንድ መጽሐፍ ስለ ኢሕአፓ ቢጽፉ የኢሕአፓ መርሕ ነበረ ማለት ትንሽነት ነው። የምትተቹበት እውቀቱና ችሎታው ካላችሁ በኦፊሴል ያወጣውን ማኒፌስቶ {ፕሮግራሙን]፤ በየወቅቱ የሚያወጣቸውን አቋሙን ተቹ።
ባልና ሚስት ተጣልተው ሽማግሌ ምክንያታቸውን ሲጠይቃቸው፤ የሚሰጡት ምላሽ እርሱ ለወር ወጪ የሚሰጠን አይበቃኝም፤ እርሷ ስገባ ፊቷን ታጠቁርብኛለች ይሆናል መልሳቸው። ዋናው ምክንያት ግን ሌላ ነው። እናንተም ዋናውን ምክንያታችሁን ለአንባብያን ሸሽጋችሁ በማይሆን ምክንያት ምስኪኑን አንባቢ አታደናግሩ።
ክርስትና ዕውነት ነው ዕውነት መስክሩ። ዕውነቱን የማታውቁት ከሆነ ደግሞ ለመጻፍ አትቸኩሉ።
Dear Dejeselam,
You are a living evidence for the inevitable freedom of our beloved church from the tribal thugs, the day time robbers, the taxi driving and parking lot bandits, the ehapa derg & woyane murderers who have been hell bent all along to disrupt, weaken and control the church so that they can spearhead their futile political agenda which usually is designed to oppress the peace loving people and pillage the country Ethiopia. I was hoping that one day Mahiber Kidusan to liberate the church from the stranglehold of the poisonous and parasite Ethiopians, unfortunately it seems that the Mahiber is spineless, dangerous, wicked, and righteous all at once just like the Lucifer. Therefore, the key lies in the hands of independent minded Ethiopians, which i thing the editor/s of this blog sphere rightly represents. Please, use it wisely.
May 21, 2010 6:08 AM "
Dear Editor (Blogger) of DejeSelam,
ከላይ፡በተመለከትው፡አስተያየት፡ላይ፡ያቀረብኩት፡
አስተያየት፡ለምን፡እስካሁን፡እንዳልወጣ፡ለመጠየቅ፡
ነው።ጽሑፌን፡እንዳይወጣ፡የሚያደርግ፡ምን፡ተገኘ
በት?!
መድኃኔ፡ዓለም፡ክርስቶስ፡ተዋሕዶ-ኢትዮጵያን፡
በምሕረቱ፡ይጎብኘን! አሜን።
ሳሙኤል፡ዘአሰቦት።