ጥቅምት አምስት ቀን ደቀ መዛሙርቱን ስብሰባ የጠሩት ዋና ዲኑ “የፈለገ ፈርሞ ይማር ያልፈለገውን አባረው” ካሉ ወዲህ ችግራቸው በኮሌጁ አስተዳደር ይኹን በቦርዱ እንደማይፈታ በመረዳት ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ማመልከታቸውን የደቀ መዛሙርቱ ተወካዮች ተናግረዋል፡፡ አቤቱታቸውን ተከትሎ በጽ/ቤቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ ውብሸት የተመራ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ሥራ አስፈጻሚ አካል ሁለት ጊዜ ወደ ኮሌጁ በመምጣት ከደቀ መዛሙርት እና ከአስተዳደር ሠራተኞች ጋራ ተወያይቷል፡፡ በዚህ ማጣራት ዋና ዲኑ ከምክትላቸው ጀምሮ ከሥራ ባልደረቦቻቸው ጋራ ተግባብተው እና ተቀናጅተው እንደማይሠሩ፤ ከሥርዐተ ትምህርት ዝግጅት ባሻገር በምግብ፣ በሕክምና በፋይል አያያዝ ሁሉ ችግሮች ስለመኖራቸው መረጋገጡ ታውቋል፡፡
ጥቅምት አምስት ቀን ደቀ መዛሙርቱን ስብሰባ የጠሩት ዋና ዲኑ “የፈለገ ፈርሞ ይማር ያልፈለገውን አባረው” ካሉ ወዲህ ችግራቸው በኮሌጁ አስተዳደር ይኹን በቦርዱ እንደማይፈታ በመረዳት ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ማመልከታቸውን የደቀ መዛሙርቱ ተወካዮች ተናግረዋል፡፡ አቤቱታቸውን ተከትሎ በጽ/ቤቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ ውብሸት የተመራ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ሥራ አስፈጻሚ አካል ሁለት ጊዜ ወደ ኮሌጁ በመምጣት ከደቀ መዛሙርት እና ከአስተዳደር ሠራተኞች ጋራ ተወያይቷል፡፡ በዚህ ማጣራት ዋና ዲኑ ከምክትላቸው ጀምሮ ከሥራ ባልደረቦቻቸው ጋራ ተግባብተው እና ተቀናጅተው እንደማይሠሩ፤ ከሥርዐተ ትምህርት ዝግጅት ባሻገር በምግብ፣ በሕክምና በፋይል አያያዝ ሁሉ ችግሮች ስለመኖራቸው መረጋገጡ ታውቋል፡፡
No comments:
Post a Comment